የሙታን ትንሣኤ

• የሙታን ትንሳኤ በሚመጣዉ ዓለም ከጌታ ጋር የምንኖረዉ ህይወት ነዉ (ፊል. 3፡10-11፣17-21) ፡፡ የሙታን ትንሳኤ ከሁሉ ይልቅ የተሻለ ተስፋ ያለዉ መሠረታዊ ትምህርት ነዉ፡፡
15.1. ትርጉም
• ለሰዎች ሁሉ አንድ ጊዜ መሞት ከዚያ በኋላ ፍርድ ተወስኖባቸዋል ይላል(ዕብ. 9፡27፣1ቆሮ.15፡22) ስለዚህ ሰዎች ከሙታን ተነስተዉ አዲስ ህይወትን ለመኖር ፍርድንም ለመቀበል የሚያገኙት ከሞት መነሳት የሙታን ተንሳኤ ይባላል ፡፡
• Anastasis (ግሪክ) Gk. (Ana= up stasis= stand = stand up)
• ትንሳኤ (geez)
15.2. ትንሳኤ ሙታን አለ
• ትንሳኤ ሙታን ባይኖር ሌሎች ስብከቶች ሁሉ ከንቱ ይሆኑ ነበር (1ቆሮ. 15፡12-19) ፡፡ ‹‹ትንሳኤ ሙታን›› መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለዉ አስተምህሮ ነው ፡፡ ‹‹ሙታን ህያዋን ይሆናሉ በድናቸዉም ይነሳል ›› (ኢሳ.26፡19) ፡፡ ‹‹ከምድር አፈር ዉስጥ ካንቀላፉት ብዙዎች ይነቃሉ፡፡
• አንዳንዶቹ ለዘላለም ህይወት ሌሎችም ለዉርደትና ለዘላለም ጉስቁልና ይነሳሉ›› (ዳን. 12፡2) ፡፡
• ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋዉ ወራት በምድር በተመላለሰባቸዉ ዓመታት ‹‹የሙታን ተንሳኤ የለም›› የሚሉ ሳዱቃዊያን ነበሩ፡፡ በመጀመሪያዋ ቤ/ክ ዘመንም ቢሆን ‹‹የሙታን ትንሳኤ የለም›› የሚሉና የሚያስተምሩም ነበሩ (ማቴ.22፡29-32፣ማር.12፡24-27፣ሉቃ. 20፡34-38፣ ዮሐ.5፡25- 29፣6፡39-54፣ 11፡24-25፣ የሐዋ.2፡24- 32፣ 13፡32-37) ፡፡
• ‹‹ክርስቶስ ከሙታን እንደተነሳ የሚሰብክ ከሆነ ግን ከእናንተ አንዳንዶቹ፡- ትንሳኤ ሙታን የለም እንዴት ይላሉ? (1ቆሮ.15፡12-19)
15.3. ሙታን እንዴት ይነሳሉ? (1ቆሮ. 15፡35-50)
• በአካለ ስጋ የሞቱ ሁሉ ድንገት ሰው ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ይነቃሉ (ይነሳሉ)፡፡ የሚነሳው ስጋዊ አካል ምን ዓይነት ይሆናል ለሚለው ከቅድመ ሞት በፊት ከነበረው አካል ፈጽሞ የተለየ ነው፡፡
15.4. የሙታን ትንሳኤ ቅደም ተከተል (1ቆሮ. 15፡23)
• የሙታን ሁሉ ትንሳኤ በአንድ ጊዜ አይሆንም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በቅደም ተከተል የሚከናወኑ የተለያዩ ትንሳኤዎች ስለመኖራቸዉ በግልጽ ያስረዳል፡፡ እነርሱም፡-
15.4.1. የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ
• ለዓለም ሁሉ ኃጢአት ቤዛ በመሆን በእንጨት ተሰቅሎ በመሞት የተቀበረዉና መጽሐፍም እንደሚል በሶስተኛዉ ቀን የተነሳዉ እርሱ የመጀመሪያና በኩር ነዉ ፡፡ ‹‹አሁን ክርስቶስ ላንቀላፉት ሁሉ በኩራት ሆኖ በእርግጥ ከሙታን ተነስቷል›› (1ቆሮ. 15፡20፣23) ፡፡
• ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በፊት በነቢያት በራሱም በክርስቶስ ኢየሱስ አገልግሎትና እንዲሁም በሐዋርያት አገልግሎት ሙታን ተነስተዋል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ከሞት የተነሱቱ ሁሉ ተመልሰዉ ሞተዋል፡፡
የእርሱ ትንሳኤ ግን ፡-
• የሞትን ጣር አጥፍቶ ዳግመኛ ላይሞትና ከዘላለም እስከ ዘላለም ህያዉ ሆኖ ይኖራል (ራዕ.1፡18) ፡፡
• በሁሉ ነገር ላይ የበላይነቱን ያሳየበት ትንሳኤ ነዉ (ቆላ.1፡18) ፡፡
እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሳቱ የተገኙ ዉጤቶች ምንድን ናቸዉ?
ሀ. ለአማኞች ሁሉ ከሞት መነሳት የታመነ ተስፋ ነዉ (1ቆሮ.15፡23)
ለ. ሞት ከእንግዲህ እርሱን ላይገዛዉ ሞትን ድል ነስቶታል (ሮሜ. 6፡8-10)
ሐ. የሞትና የሲኦል መክፈቻ በእጁ ሆኗል (ራዕ. 1፡18)
መ. በሞት ላይ ስልጣን ያለዉን ዲያቢሎስን ሽሮታል (ዕብ. 2፡14)
ሠ. እኛ ዳግመኛ ተወልደን ለህያዉ ተስፋ በቅተናል (1ጴጥ. 1፡3-5)
15.4.2. የቅዱሳን ትንሳኤ
ይህኛዉ ትንሳኤ የትንሳኤ በኩር ከሆነዉ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በመቀጠል ሐዋርያዉ ጳዉሎስ ‹‹የክርስቶስ የሆኑት›› በማለት የገለጻቸዉ የሚነሱበት ትንሳኤ ነዉ (1ቆሮ.15፡23) ፡፡
በዚህኛዉ ትንሳኤ ጌታችን ኢየሱስ ቤተክርስቲያንን ለመዉሰድ ሲመለስ በእርሱ አምነዉ የሞቱት ቅዱሳን አስቀድመዉ ይነሳሉ፣ በህይወት ያሉት ደግሞ ስጋቸዉ በክብር ተለዉጦ በአንድነት ጌታን በአየር ላይ ለመቀበል በደመና ይነጠቃሉ (1ቆሮ. 15፡51-53፣ 1ተሰ. 4፡13-18) ፡፡
ሀ. የቅዱሳን ትንሳኤ
– የጻድቃን ትንሳኤ (ሉቃ.14፡14)
– የህይወት ትንሳኤ (ዮሐ.5፡29)
– የትንሳኤ ልጆች እና የእግዚአብሔር ልጆች (ሉቃ.20፡36) ትንሳኤ ተብሎ ተጠርቷል፡፡
ይህ የቅዱሳን ትንሳኤ በመቀጠል ከሚሆነዉ ከኃጢአን ትንሳኤ አንጻር የፊተኛዉ ትንሳኤ ተብሏል (ራዕ.20፡1-6) ፡፡
ለ. የቅዱሳን ትንሳኤ ዓላማ
የቅዱሳን ትንሳኤ፡
1. ክቡር የሆነዉን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ስጋ እንዲመስል፣ የሚሞተዉና የሚበሰብሰዉ ስጋችን ተለዉጦና ሞት ዳግመኛ የማይገዛዉን የትንሳኤን አካል ለብሰን ወደሰማይ አገራችን ለመሄድ ብቁ ያደርገናል(1ቆሮ.15፡51-54፣ ፊል.3፡21፣ ዮሐ.14፡1-3) ፡፡
2. ቅዱሳን በምድር ህይወታቸዉ በመንግስቱ ዉስጥ ላበረከቱት አስተዋጽኦና ለደከሙበት ስራ ከጌታ ዘንድ ዋጋንና ሽልማትን ይቀበላሉ (ሉቃ. 14፡14፣ 1ቀሮ. 3፡14 ራዕ. 22፡12-15፣17፣20)
በታማኝነት ሲያገለግሉት የቆዩትንና የሚቆዩትን በዚያን ጊዜ ብድራታቸዉን (rewards) ጌታ ይከፍላቸዋል (ሉቃ. 12፡35-48 ፣ 2ጢሞ.4፡6-8 ‹‹ያን ቀን››) ፡፡
2. ጌታ በቅዱሳን ጠላት ላይ ሊበቀልና ለቅዱሳኑ በጽድቅ ሊፈርድ የቅዱሳን ትንሳኤን አዘጋጀ (1.ቆሮ.15፡54-58፣ኢሳ. 63፡4) ፡፡ “For the day of vengeance is in my heart, and the year of my redeemed has come” (መዝ.50፡1-6፣ራዕ.6፡9-17፣14፡14- 20፣ ማቴ.13፡30፣ ማቴ.24፡29-31 ሉቃ.17፡22-37 2ተሰ.1፡7-10) ፡፡
4. የቤተክርስቲያን ሰርግና የበጉ ሰርግ እራት ይሆናል (ራዕ. 19፡7-9) ፡፡
5. ከታላቁ መከራ ዘመን ቁጣ ቅዱሳን ይድናሉ (ራዕ. 3፡10 (ራዕ. 6-19) ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ስለመጨረሻዉ ዘመን ሲያስተምር ስለታላቁ መከራ እንዲህ በማለት ገልጾታል፡፡
‹‹በዚያን ጊዜ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ሆኖ የማያዉቅ ከዚያም በኋላ የሚስተካከለዉ የሌለ ታላቅ መከራ ይሆናል›› (ማቴ. 24፡21) ፡፡ ታላቁ መከራ የተባለበትም ከአሁን በፊት ሆኖ የማያዉቅ ታላቅ የመከራ ጊዜ ስለሚሆን ነዉ (ዳን. 12፡1) ፡፡
የታላቁ መከራ ዘመን ለ7 ዓመት እንደሚሆን መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፡፡ ቅዱሳን (ቤተክርስቲያን) ይህ የ7 ዓመቱ ታላቅ መከራ ዉስጥ ያልፋሉ? ወይስ አያልፉም? ለሚለዉ ጥያቄ የተለያዩ አመለካከቶች ወይም አቋሞች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ እነዚህም፡- ቅድመ ፣ አጋማሽ እና ድህረ መከራ አመለካከቶች ናቸዉ፡፡ ይሁን እንጂ ከሚከተሉት ምክንያቶች (መጽሐፍ ቅዱሳዊ) በመነሳት
ቤተክርስቲያን በሰባቱ ዓመታት የመከራ ጊዜ ዉስጥ አታልፍም ብለን ማመን እንችላለን፤
ሀ. ታላቁ መከራ ከተጠቀሰበት የራዕይ መጽሐፍ (ከምዕ.5 እስከ ምዕ. 19 ድረስ) የቤ/ክ ስም አንድም ቦታ ተጠቅሶ አናገኝም፡፡ ከምዕ.1 – 4፡20 ብቻ ቤ/ክ ተጠቅሳለች ፡፡
ለ. ለቤተክርስቲያን የመዳን ተስፋ ተሰጥቷታል (ራዕ. 3፡10) እንጂ የመከራና የቁጣ ቀጠሮ አልተሰጣትም (ዮሐ. 3፡36፣1ተሰ.5፡9፣ ዮሐ. 14፡1-3) ፡፡
ሐ. ከእግዚአብሔር ባህሪይ እንደምንረዳዉም ፍርድ ከመገለጹ በፊት አስቀድሞ ጌታ ኢየሱስ ልጆቹን ያወጣቸዉ ነበር ፤ ሎጥ (ዘፍ. 19፡22) ፣ ኖህም ቢሆን ከጥፋት ዉኃ በፊት (ዘፍ.7፡1-4)፣(ራዕ. 4፡1፣ 11፡12- 14) ፡፡
6. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛ ተመልሶ ለሺህ ዓመት በምድር ላይ ይነግሳል፡፡ እርሱ ለሺህ ዓመት መንግስቱን በዚህ ምድር ላይ መስርቶ ሲነግስ ከእርሱ ጋር ቅዱሳን ለሺህ ዓመት በምድር ላይ አብረው ይነግሳሉ (ራዕ. 20፡1-10 (4-5) ፡፡
• በሺህ ዓመት መንግስት
ሀ. ሰይጣን ተይዞ ለሺህ ዓመት ይታሰራል፡፡
ለ. ቅዱሳን (የብ/ኪ እና የታላቁ መከራ ቅዱሳን) ከክርስቶስ ጋር 1000 ዓመት በምድር ላይ ይነግሳሉ (ሚኪ. 4፡1-2 ኢሳ፡2፡1-4) ፡፡
• የሺህ ዓመት መንግስት ባህሪያት
1. እርግማን ከምድር ላይ ሙሉ በሙሉ ይነሳል፡፡
• ምድር ሁሉ ፍሬያማ ትሆናለች (ኢሳ. 35፡1-2 ) ፡፡
2. ፍጹም ሰላም በምድር ላይ ይሆናል፡፡
• የሰላሙ አለቃ የሚገዛበት ፣ ጠላት ዲያብሎስ የሌለበት ጦርና፣ የጦር ወሬ የማይሰማበት፣ ይልቁንም የጦር መሳሪያዎች የልማት መሳሪያዎች ሆነዉ የሚለወጡበት ይሆናል (ሚኪ. 4፡1-3፣ኢሳ.2፡1-4፣9፡7፣ዘካ. 9፡10) ፡፡
• በእንስሳት መካከል እንኳን ፍጹም ሰላም ይሰፍናል (ኢሳ.11፡6-9፣65፡25)፡፡
• ፍጥረት ከጥፋት ባርነት ነጻ ይወጣል (ሮሜ. 8፡19-22) ፡፡
3. የሰዉ እድሜ በምድር እጅግ ይረዝማል (ኢሳ. 65፡22) ፡፡
4. አይሁዶች ወደ እየሩሳሌም ይሰበሰባሉ፤
• የመንግስቱ ማዕከል በዚህ በኢየሩሳሌም ከተማ ይሆናል፡፡
• መቅደሱ እንደገና ይገነባል (የፈረሰዉ የዳዊት ድንኳን እንደገና ይሰራል)
(ሚኪ.4፡8 አሞ. 3፡11-12) ፡፡
15.4.3. የኃጥአን ትንሳኤ
በመጨረሻም ክርስቶስን ሳይለብሱ ያልዳኑና ስማቸዉ በህይወት መዝገብ ዉስጥ ተጽፎ ያልተገኘ ሁሉ ለፍርድ ይነሳሉ (ራዕ. 20፡5) ፡፡ ይህ የመጨረሻዉ የኃጢአን ትንሳኤ የሚሆነዉ ከሺህ አመት መንግስት በኋላ የሚሆን ነዉ (ራዕ. 20፡5፣11-15) ፡፡
ሀ. የኃጥአን ትንሳኤ ዓላማ ፡-
1. በስሙ በመጠመቅ የኃጢአትን ስርየት ባለማግኘታቸዉ የኃጢአትና የስራቸዉን ደመወዝ የሆነዉን የዘላለም ሞትን ይቀበላሉ (ሮሜ. 6፡23)
2. ለዘላለም ከእግዚአብሔር ተለይተዉ የዘላለም የገሃነም እሳት ፍርድን ተቀብለዉ ለሰይጣንና ለወደቁት መላዕክት ወደተዘጋጀዉ ስፍራ ለዘላለም ወደሚሰቃዩበት፣ እሳቱ ወደማይጠፋበትና ትሉ ወደማይሞትበት ወደ ዘላለም ጉስቁልና አልፈዉ ይሰጣሉ (ማቴ. 25፡41-46፣ራዕ.20፡11-15) ፡፡

Published by

wongelu

Name: Wongelu Woldegiorgis Nationality: Ethiopian Profession: Naturopathic Doctor Nutritionist Accountant Entrepreneur Formulator of beauty and wellness products Consultant for business development and legal documentation Education: BSc in Acvounting, Master’s Degree in Nutrition, Marketing Management . Honorary Doctorate from Abyssinia, Ethiopia PHD Naturopathic Medicine – Languages: Amharic, English, Swahili Personal Qualities: Honest, adaptable, good communicator, spiritually devoted, passionate about natural health and community development Church Involvement: Active in Apostolic Church International Fellowship Limited (ACIF Uganda) Talents: Translation, teaching, preaching, and serving in children's ministry Preparing curriculum and lesson plans based on Oneness Apostolic doctrine Other Interests: Passionate about fitness and bodybuilding Pursuing online work in writing, translation, virtual assistance, and e-commerce

One thought on “የሙታን ትንሣኤ”

  1. ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ይባርክህ ከዚህ በባላጣ የቃሉን ብርሃን ያብራልህ በጣም ተጠቅሜበታለሁ መልክቶችህ እንደገና ያብዛልህ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *