ሁሉን አውቃለሁ ማለት የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው

አውቃለሁ እንደሚል ሰው የሚያስፈራ ሰው የለም፡፡ አውቃለሁ የሚል ሰው ለመማር ምንም ስፍራ የለውም፡፡ አውቃለሁ የሚል ሰው ለመማር ፈቃደኛ አይደለም፡፡ አውቃለሁ የሚል ሰው ለመሻሻል ምንም ቦታ የለውም፡፡ አውቃለሁ የሚል ሰው ማደግ አቁሟል፡፡ ሁሉንም አውቃለሁ የሚል ሰው ለመለወጥ ተስፋ የለውም፡፡
ለራሱ ጠቢብ የሆነ የሚምስለውን ሰው አየኸውን? ከእርሱ ይልቅ ለሰነፍ ተስፋ አለው። ምሳሌ 26፡12
ሁሉን አውቃለሁ ማለት የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ሁላችንም እየተማርን ነው፡፡ ለመማር እስከተዘጋጀን ድረስ ሁል ጊዜ እንማራለን፡፡ ለመማር እስከፈቀድን ድረስ የምንማራቸው እጅግ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ እያንዳንዱ ሰው በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ በእውቀት ይበልጠናል፡፡ ከማንም ሰው ለመማር ፈቃደኛ ከሆንን ማንም ሰው ሊያስተምረንና በህይወታችን ላይ ዋጋን ሊጨምር ይችላል፡፡ ሁልጊዜ የሚማር ልብ ካለን በማንም ሰው አማካኝነት ለህይወታችን መለወጥ የሚጠቅም ቁልፍ ነገር ልንማር እንችላለን፡፡
ሰው ባወቀ መጠን የሚያውቀው ማወቅ የሚገባውን ያህል አንደማያውቅ ነው፡፡
ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 8፡2

Published by

wongelu

Name: Wongelu Woldegiorgis Nationality: Ethiopian Profession: Naturopathic Doctor Nutritionist Accountant Entrepreneur Formulator of beauty and wellness products Consultant for business development and legal documentation Education: BSc in Acvounting, Master’s Degree in Nutrition, Marketing Management . Honorary Doctorate from Abyssinia, Ethiopia PHD Naturopathic Medicine – Languages: Amharic, English, Swahili Personal Qualities: Honest, adaptable, good communicator, spiritually devoted, passionate about natural health and community development Church Involvement: Active in Apostolic Church International Fellowship Limited (ACIF Uganda) Talents: Translation, teaching, preaching, and serving in children's ministry Preparing curriculum and lesson plans based on Oneness Apostolic doctrine Other Interests: Passionate about fitness and bodybuilding Pursuing online work in writing, translation, virtual assistance, and e-commerce

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *