ልብህ የሚሄደው መዝገብህ ባለበት ቦታ ነው፡፡ ሰው በተፈጥሮው ሃብቱና ልቡ ተነጣጠለው አይኖሩም፡፡ መዝገብህ ባለበት ልብህ በዚያ ይሆናል፡፡
መዝገብህ በሌለበት ቦታ ልብህ በዚያ አይኖርም፡፡ ትኩረትህ ሁሉ የሚኖረው የኔ የምትለው የምትጠነቀቅለት ነገር ባለበት ቦታ ነው፡፡ ስለዚህ አለ ኢየሱስ ልባችሁ በሰማይ እንዲያተኩር ወሳኙ መንገድ ፣ ልባችሁ በሰማይ እንዲቀር የሚረዳው ነገር ፣ ልባችሁ በሰማይ ትኩረት እንዲያዝ ከፈለጋችሁ መዝገባችሁን በሰማይ አስቀምጡ እያለን ነው፡፡
በምድር ላይ የምንደገፍበት ነገር ሲጠፋ ልባችን ወደ ሰማይ መዝገብ ያዘነብላል፡፡ ነገር ግን የምድር ሃብታችን ሲበዛና በዚያም ለመታመን ስንፈተን ልባችንም በምድር ላይ ይቀራል፡፡ ልባችንን የምንጥልበት ሃብታችን በምድር ላይ እየበዛ በሄደ መጠን ልባችን ከሰማይ ላይ እየተነሳ ይሄዳል፡፡ መዝገባችን በምድር ሲሆን ልባችንም በምድር ይሆናል፡፡ መዝገባችን በሰማይ ሲሆን በቅፅበት ልባችንም በሰማይ ይሆናል፡፡
ብዙ ጊዜ ልባችን ከሰማይ በመነሳት እንፈተናልን፡፡ በዚህ ፈተና ያለመውደቅ መንገዱን ኢየሱስ ያስተምራል፡፡ መዝገብን በምድር የመሰብሰብ ጉዳቱ ልባችንን ከሰማይ ላይ እንዲነሳ ሰማይ ትኩረታችን እንዳይሆን ያደርጋል፡፡ መዝገብን በሰማይ የመሰብሰብ ጥቅሙ ልባችንን በሰማይ ይሰበስብልናል፡፡
ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ መዝገብ አትሰብስቡ፤ ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና። ማቴዎስ 6፡19-21
Published by
wongelu
Name: Wongelu Woldegiorgis
Nationality: Ethiopian
Profession:
Naturopathic Doctor
Nutritionist
Accountant
Entrepreneur
Formulator of beauty and wellness products
Consultant for business development and legal documentation
Education:
BSc in Acvounting,
Master’s Degree in Nutrition, Marketing Management .
Honorary Doctorate from Abyssinia, Ethiopia
PHD Naturopathic Medicine –
Languages: Amharic, English, Swahili
Personal Qualities: Honest, adaptable, good communicator, spiritually devoted, passionate about natural health and community development
Church Involvement:
Active in Apostolic Church International Fellowship Limited (ACIF Uganda)
Talents: Translation, teaching, preaching, and serving in children's ministry
Preparing curriculum and lesson plans based on Oneness Apostolic doctrine
Other Interests:
Passionate about fitness and bodybuilding
Pursuing online work in writing, translation, virtual assistance, and e-commerce
View all posts by wongelu