. እግዚአብሔርን ፍለጋ – ቀጣይ፡-
ምኑን ነው የምንፈልገው?፡-
ባለፈው ክፍል – እግዚአብሔርን ፍለጋ በሚል – ስለእግዚአብሔር መኖር በተፈጥሮ፣ በሕሊና፣ በመሳሰሉት ማረጋገጥ እንደሚቻል አይተናል።
በአሁኑ ጊዜ የፈጣሪን /የእግዚአብሔርን መኖር የሚጠራጠር ብዙም ላይኖር ይችላል፤ ወይም በአሁኑ ጊዜ ለኛ ይህ ብዙም አሳሳቢ ጥያቄ አይደለም።
ከላይ ከተጠቀሱት በአንዱ ወይም በሌላ በሆነ መንገድ – የእግዚአብሐየርን መኖር አረጋገጥን – እግዚአብሔርን አገኘነው። ካገኘነው በኋላ ምኑን ነው ማየት የምንፈልገው? ስንል ዳዊት እንዲህ ይለናል፡-
ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። መዝ ፻፬/፻፭፣ ፬
– የእግዚአብሔር ሕልውና /መኖሩ/ የሚረጋገጠው አንድ ጊዜ ነው። ከተገኘ – አለ። አይጠፋም።
ከዚያ በኋላ ግን ሁልጊዜ መፈለግ ያለብን – ፊቱን – ነው።
– በምናያቸው ፍጥረታት የእግዚአብሔርን አስደቂ ኃያል እጅ እናያለን። ቀጥሎ ግን ሁልጊዜ ፊቱን ማየት አለብን።
ፊት ምንድን ነው? -የማንነት መለያ ነው። ሁላችንም የምንለየው በፊታችን ነው። መታወቂያ ላይ የሚደረገው ፎቶ – ጉርድ ፎቶ – የሚያሳየው ፊታችንን ነው።
– አንድን ሰው አየሁት ለማለት – ፊቱን – ማየት ግድ ነው።
– ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ሕዝቡን ነጻ አውጥቶ ሲመራ፣ በተአምራት ብዙ ዘመን ከኖረ በኋላ፡- እግዚአብሔርን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡-
o እርሱም፦ እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለ።….
– እግዚአብሔርም –
o …ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም……ፊቴ ግን አይታይም» አለ። ዘጸ ፴፫፡ ፲፯ – ፳፫።
– ፊቱን ማየት የማይቻል ከሆነ -ፊቱ የማይታይ ከሆነ – ለምን ፊቱን ፈልጉ ተባለ? – ማየት የማይቻለው በዚህ በሥጋ ዓይን ነው። እግዚአብሔር መንፈስ ነውና።
– በመንፈስ ግን ከእኛ ጋራ ሲሆን፣ ሲሠራ፣ ሕይወታችን ሲጠብቅ… እናየዋለን።
ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም። (የሐዋ ፲፯፣ ፳፮)
– መምህራን እንደሚያስተምሩት በርግጥ የሙሴ ጥያቄ ተመልሷል፤ ነገር ግን የተመለሰው ከ1400 ዓመት በኋላ- በኢየሱስ ክርስቶስ – በደብረ ታቦር ነው።
o ሙሴ በጥየቄው መሰረት በዓይነ-ሥጋ በአካል እግዚአብሔርን ያየው – በኢየሱስ ክርስቶስ – ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋ የተገለጠው አግዚአብሔር ነውና።
በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ማቴ ፲፯፣ ፪ – ፫
ዛሬም እኛ እግዚአብሔርን በመንፈስ ዓይን የምናየው – በኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ስለዚህ፡-
፭. የፍለጋው ማብቂያ – ኢየሱስ ክርስቶስ
o በተሰጠን አእምሮ በምናደርገው ምርምር በተፈጥሮ፣ በኅሊና.. ፈጣሪ እንዳለ እናውቃለን። ፍጥረታትን ሁሉ እግዚአብሔር እንደፈጠራቸው እንዳስገኛቸው እንደሚቆጣጠራቸው እንረዳለን።
o እግዚአብሔርን ፍለጋ የምናደርገው ጥረት እግዚአብሔር እንዳለ እንድናውቅ እንጂ ከእግዚአብሔር ጋር እንድንገናኝ አያደርገንም።
o ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኘው በእኛ ፍለጋ ሳይሆን በእርሱ ፍለጋ ነው። እርሱ እኛን ስለፈለገን። ስለዚህ የእኛ እግዚአብሔርን ፍለጋ የሚጠናቀቀው በራሱ በእግዚአብሔር ፍለጋ ነው።
– የእግዚአብሔር ፍለጋ – ፍለጋው አያልቅም – እንደምንለው አይደለም። መድረሻ አለው። የእግዚአብሔር ፍለጋ ማብቂያው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
እኛ እርሱን ልንደርስበት ስለማንችል እርሱ እኛን ፈለገን። በሚገባን በምናውቀው ባሕርይ። በሰው – ሰው ሆኖ ሊፈልገን መጣ።
የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው። ሉቃ ፲፱፣ ፲
መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው። ዮሐ ፩፣ ፲፰።
ተረከው – ማለት የቃል ትረካ አይደለም፤ በተግባር በኑሮ፣ በሕይወት፣ በሞት፡በትንሣኤ… ገለጠው ማለት ነው።
ክርስቶስን ስናገኝ / ክርስቶስ ሲያገኘን/ ያን ጊዜ እግዚአብሔርን አገኘነው – አወቅነው፡ ማለት ነው።
ማጠቃለያ፡- እግዚአብሔር አንዲህ አለ / ብሎ ተናገረ፣ ከማለታችን በፊት እግዚአብሔር አለ /መኖሩን/ እንበል።
– እግዚአብሔር አለ/የለም በሚል ክርክር አንዱ ፈላስፋ የቆሎ ተማሪን ሲጠይቀው፣ እነዲህ መለሰለት፡ «እግዚአብሔርን አለ ብለኽው ባይኖር ችግር የለውም፤ የለም ብለኽው ካለ ግን ወዮልህ።»
– አንዳንድ ወገኖች – ከባድ ችግር ሲገጥማቸው ወይም ያልሆነ መጥፎ ነገር ሲያዩ «እግዚአብሔርማ የለም፤ በእውነት ቢኖር እንደዚህ አይሆንም ነበር፤ » ይላሉ።
– እግዚአብሔር አንድን ነገር ለምን እንደሚያደርግ፣ እንዴት እንደሚሠራ ለእኛ ሁሉም ነገር ግልጽ ላይሆን ይችላል። ዝም ብለን በትዕግስት እንጠብቀው፤
እንደሚባለው አንዳንድ ነገሮች በጣም እንግዳ ይሆናሉ፤ ለምን እንዲህ ይሆናል አንበል፤ ቃሉ እንደሚል፡-
ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው። ዘዳ ፳፱፣ ፳፱
– ያለማቋረጥ ፀሐይን የሚያወጣት/የሚያገባት፣ ዝናቡን የሚያዘንብ፣ አዝመራውን የሚያበቅል፣ ለፍሬ የሚያደርስ፣ ሁሉን የሚመግበው ፣ የሚያስተዳድረው አምላክ – አለ።
– እኛንም ወደዚች ምድር ያመጣን፣ የፈጠረን ነው እርሱ የሚያኖረን ። አንጨነቅ።
– በእውነት እግዚአብሔር አለ ። ከሁሉም በላይ ትልቅ መጽናኛችን ነው።
o መኖሩን ያመንነውን – ፈልገን ያገኘነውን ወይም በትክክል ለመናገር ፈልጎን ያገኘንን / እንድናገኘው የተፈለገውን/ መተዋወቅ ቀጣዩ ተገቢ ጉዳይ ነው ። ስንተዋወቅ የምንለዋወጠው ስምን ነው? — እገሌ እባላለሁ።- –
o ስለዚህ ይህ ፈጣሪ ማን ይባላል?….
o የእግዚአብሔር ስም.. ይቀጥላል
Thinkyou