እግዚአብሔርን ማወቅ – ክፍል …..7…..


. እግዚአብሔርን ፍለጋ – ቀጣይ፡-
ምኑን ነው የምንፈልገው?፡-

ባለፈው ክፍል – እግዚአብሔርን ፍለጋ በሚል – ስለእግዚአብሔር መኖር በተፈጥሮ፣ በሕሊና፣ በመሳሰሉት ማረጋገጥ እንደሚቻል አይተናል።

በአሁኑ ጊዜ የፈጣሪን /የእግዚአብሔርን መኖር የሚጠራጠር ብዙም ላይኖር ይችላል፤ ወይም በአሁኑ ጊዜ ለኛ ይህ ብዙም አሳሳቢ ጥያቄ አይደለም።

ከላይ ከተጠቀሱት በአንዱ ወይም በሌላ በሆነ መንገድ – የእግዚአብሐየርን መኖር አረጋገጥን – እግዚአብሔርን አገኘነው። ካገኘነው በኋላ ምኑን ነው ማየት የምንፈልገው? ስንል ዳዊት እንዲህ ይለናል፡-

ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። መዝ ፻፬/፻፭፣ ፬

– የእግዚአብሔር ሕልውና /መኖሩ/ የሚረጋገጠው አንድ ጊዜ ነው። ከተገኘ – አለ። አይጠፋም።

ከዚያ በኋላ ግን ሁልጊዜ መፈለግ ያለብን – ፊቱን – ነው።

– በምናያቸው ፍጥረታት የእግዚአብሔርን አስደቂ ኃያል እጅ እናያለን። ቀጥሎ ግን ሁልጊዜ ፊቱን ማየት አለብን።

ፊት ምንድን ነው? -የማንነት መለያ ነው። ሁላችንም የምንለየው በፊታችን ነው። መታወቂያ ላይ የሚደረገው ፎቶ – ጉርድ ፎቶ – የሚያሳየው ፊታችንን ነው።

– አንድን ሰው አየሁት ለማለት – ፊቱን – ማየት ግድ ነው።

– ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ሕዝቡን ነጻ አውጥቶ ሲመራ፣ በተአምራት ብዙ ዘመን ከኖረ በኋላ፡- እግዚአብሔርን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡-

o እርሱም፦ እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለ።….

– እግዚአብሔርም –

o …ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም……ፊቴ ግን አይታይም» አለ። ዘጸ ፴፫፡ ፲፯ – ፳፫።

– ፊቱን ማየት የማይቻል ከሆነ -ፊቱ የማይታይ ከሆነ – ለምን ፊቱን ፈልጉ ተባለ? – ማየት የማይቻለው በዚህ በሥጋ ዓይን ነው። እግዚአብሔር መንፈስ ነውና።

– በመንፈስ ግን ከእኛ ጋራ ሲሆን፣ ሲሠራ፣ ሕይወታችን ሲጠብቅ… እናየዋለን።

ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም። (የሐዋ ፲፯፣ ፳፮)

– መምህራን እንደሚያስተምሩት በርግጥ የሙሴ ጥያቄ ተመልሷል፤ ነገር ግን የተመለሰው ከ1400 ዓመት በኋላ- በኢየሱስ ክርስቶስ – በደብረ ታቦር ነው።

o ሙሴ በጥየቄው መሰረት በዓይነ-ሥጋ በአካል እግዚአብሔርን ያየው – በኢየሱስ ክርስቶስ – ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋ የተገለጠው አግዚአብሔር ነውና።
በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ማቴ ፲፯፣ ፪ – ፫
ዛሬም እኛ እግዚአብሔርን በመንፈስ ዓይን የምናየው – በኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

ስለዚህ፡-


፭. የፍለጋው ማብቂያ – ኢየሱስ ክርስቶስ

o በተሰጠን አእምሮ በምናደርገው ምርምር በተፈጥሮ፣ በኅሊና.. ፈጣሪ እንዳለ እናውቃለን። ፍጥረታትን ሁሉ እግዚአብሔር እንደፈጠራቸው እንዳስገኛቸው እንደሚቆጣጠራቸው እንረዳለን።

o እግዚአብሔርን ፍለጋ የምናደርገው ጥረት እግዚአብሔር እንዳለ እንድናውቅ እንጂ ከእግዚአብሔር ጋር እንድንገናኝ አያደርገንም።

o ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኘው በእኛ ፍለጋ ሳይሆን በእርሱ ፍለጋ ነው። እርሱ እኛን ስለፈለገን። ስለዚህ የእኛ እግዚአብሔርን ፍለጋ የሚጠናቀቀው በራሱ በእግዚአብሔር ፍለጋ ነው።

– የእግዚአብሔር ፍለጋ – ፍለጋው አያልቅም – እንደምንለው አይደለም። መድረሻ አለው። የእግዚአብሔር ፍለጋ ማብቂያው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።


እኛ እርሱን ልንደርስበት ስለማንችል እርሱ እኛን ፈለገን። በሚገባን በምናውቀው ባሕርይ። በሰው – ሰው ሆኖ ሊፈልገን መጣ።
የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው። ሉቃ ፲፱፣ ፲

መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው። ዮሐ ፩፣ ፲፰።

ተረከው – ማለት የቃል ትረካ አይደለም፤ በተግባር በኑሮ፣ በሕይወት፣ በሞት፡በትንሣኤ… ገለጠው ማለት ነው።

ክርስቶስን ስናገኝ / ክርስቶስ ሲያገኘን/ ያን ጊዜ እግዚአብሔርን አገኘነው – አወቅነው፡ ማለት ነው።

ማጠቃለያ፡- እግዚአብሔር አንዲህ አለ / ብሎ ተናገረ፣ ከማለታችን በፊት እግዚአብሔር አለ /መኖሩን/ እንበል።

– እግዚአብሔር አለ/የለም በሚል ክርክር አንዱ ፈላስፋ የቆሎ ተማሪን ሲጠይቀው፣ እነዲህ መለሰለት፡ «እግዚአብሔርን አለ ብለኽው ባይኖር ችግር የለውም፤ የለም ብለኽው ካለ ግን ወዮልህ።»

– አንዳንድ ወገኖች – ከባድ ችግር ሲገጥማቸው ወይም ያልሆነ መጥፎ ነገር ሲያዩ «እግዚአብሔርማ የለም፤ በእውነት ቢኖር እንደዚህ አይሆንም ነበር፤ » ይላሉ።

– እግዚአብሔር አንድን ነገር ለምን እንደሚያደርግ፣ እንዴት እንደሚሠራ ለእኛ ሁሉም ነገር ግልጽ ላይሆን ይችላል። ዝም ብለን በትዕግስት እንጠብቀው፤

እንደሚባለው አንዳንድ ነገሮች በጣም እንግዳ ይሆናሉ፤ ለምን እንዲህ ይሆናል አንበል፤ ቃሉ እንደሚል፡-

ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው። ዘዳ ፳፱፣ ፳፱

– ያለማቋረጥ ፀሐይን የሚያወጣት/የሚያገባት፣ ዝናቡን የሚያዘንብ፣ አዝመራውን የሚያበቅል፣ ለፍሬ የሚያደርስ፣ ሁሉን የሚመግበው ፣ የሚያስተዳድረው አምላክ – አለ።

– እኛንም ወደዚች ምድር ያመጣን፣ የፈጠረን ነው እርሱ የሚያኖረን ። አንጨነቅ።

– በእውነት እግዚአብሔር አለ ። ከሁሉም በላይ ትልቅ መጽናኛችን ነው።

o መኖሩን ያመንነውን – ፈልገን ያገኘነውን ወይም በትክክል ለመናገር ፈልጎን ያገኘንን / እንድናገኘው የተፈለገውን/ መተዋወቅ ቀጣዩ ተገቢ ጉዳይ ነው ። ስንተዋወቅ የምንለዋወጠው ስምን ነው? — እገሌ እባላለሁ።- –

o ስለዚህ ይህ ፈጣሪ ማን ይባላል?….

o የእግዚአብሔር ስም.. ይቀጥላል

Published by

wongelu

Name: Wongelu Woldegiorgis Nationality: Ethiopian Profession: Naturopathic Doctor Nutritionist Accountant Entrepreneur Formulator of beauty and wellness products Consultant for business development and legal documentation Education: BSc in Acvounting, Master’s Degree in Nutrition, Marketing Management . Honorary Doctorate from Abyssinia, Ethiopia PHD Naturopathic Medicine – Languages: Amharic, English, Swahili Personal Qualities: Honest, adaptable, good communicator, spiritually devoted, passionate about natural health and community development Church Involvement: Active in Apostolic Church International Fellowship Limited (ACIF Uganda) Talents: Translation, teaching, preaching, and serving in children's ministry Preparing curriculum and lesson plans based on Oneness Apostolic doctrine Other Interests: Passionate about fitness and bodybuilding Pursuing online work in writing, translation, virtual assistance, and e-commerce

One thought on “እግዚአብሔርን ማወቅ – ክፍል …..7…..”

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *