መንፈሳዊ ስጦታዎችና ተፈጥሯዊ ችሎታዎች
መንፈሳዊ ስጦታዎችና ተፈጥሮአዊ ችሎታዎች የሚመሳሰሉበት ነገር ቢኖርም አንድ ዓይነት ግን አይደሉም፡፡ ወንዶችና ሴቶች በተፈጥሮአቸው እንደሚለያዩ ሁሉ ተፈጥሮአዊ ችሎታዎችና መንፈሳዊ ስጦታዎች ራሱን የቻለ ልዩነት አላቸው፡፡ እርግጥ ነው የሁለቱም ምንጭ እግዚአብሔር ነው፣ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ሊመሳሰሉ የሚችሉበት ሁኔታ አለ፡፡ ይሁን እንጂ ተፈጥሮአዊ ልደትና ዳግም ልደት እንደሚለያዩ ሁሉ መንፈሳዊ ስጦታዎችና ተፈጥሮአዊ ችሎታዎች የዚያኑ ያህል ይለያያሉ፡፡ ባመኑትና ባለመኑት መካከል ያለውን ልዩነት በግልጽ የሚያስገነዝቡን መንፈሳዊ ስጦታዎች ናቸው፡፡ መንፈሳዊ ስጦታዎች ያመነ ሰው እድል ፈንታ ናቸው፡፡ መንፈሳዊ ስጦታዎች ለአማኙ በክርስቶስ አካል ውስጥ ሥፍራን ይሰጡታል፡፡ ያለእነዚህ ስጦታዎች አማኝ የተጣለበትን አደራ በቀላሉ አይገነዘብም፡፡ ስለ ልዩነታቸው እንዲህ ብንናገርም የሚገናኙበት ሁኔታ የለም ማለት ግን አይቻልም፡፡
ግንኙነታቸው
1ኛ. የሁለቱም ምንጭ እግዚአብሔር መሆኑ፣ እግዚአብሔር በተፈጥሮአችን ውስጥ ለተቀመጡ ልዩ ልዩ ችሎታዎቻችን ምንጭ ነው፡፡ ማንም ለራሱ ያንን ማድረግ አይቻለውም፡፡ ተፈጥሮአዊ ችሎታዎቻችን በስልጠና ቢዳብሩም በምርጫችን የኛ ልናደርጋቸው አንችልም፡፡ ድምጻችንን፣ በባሕሪያችን ውስጥ የተቀመጡ ልዩ ልዩ የማንነቶቻችን መግለጫዎች የመነጩት ከሰጪው ነው፡፡
2ኛ. ተፈጥሮአዊ ችሎታዎች ለበጎ ምግባር የሚውሉ መሆናቸው፣ በተፈጥሮ ችሎታችን ውስጥ የተቀመጡ አንዳንድ ተሰጥኦዎች እግዚአብሔር በአማኙ ውስጥ ለሚሠራው ሥራ አመቺ ሁኔታን ይፈጥራሉ፡፡ ለምሳሌ ድምጻቸው መረዋ የሆኑ ሰዎች ዘፋኝ ሆነው ያገለገሉትን ያህል ዘማሪ ሆነው ሊያገልገሉ የሚችሉበት ሁኔታ መፈጠሩ፣ በባህሪያቸው ለጋስ የሆኑ ሰዎች የምህረት አድራጊነት ጸጋ በውስጣቸው ሊሠራ መቻሉ፣ ተናጋሪና ፀሐፊ የሆኑ ሰዎችን ሰባኪና መምህራን ለመሆን መቻላቸው ከብዙ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ፡፡
መንፈሳዊ ስጦታዎች
የጸጋ ስጦታዎች ስማቸው እንደሚያመለክተው እግዚአብሔር ከርህራሄው የተነሳ ቅጣት ለሚገባቸው ሰዎች ያደረገው ልግስናዎች ናቸው፡፡ ሁሉም አማኞች የዚህ እድል ፈንታ ተካፋይ ናቸው፡፡
ይሁን እንጂ ስጦታውን የሚቀበሉና በአግባቡ የሚያስተናግዱ ብዙ አይደሉም፡፡ መንፈሳዊ ስጦታዎች ለተቀባዩ ጥቅምና መታነጽ የተሰጡ ቢሆንም አውራ ግባቸው የክርስቶስን አካል ማነቃቃትና መገንባት ነው፡፡ ስለ ስጦታ በተጠቀሰባቸው አራቱ የአዲስ ኪዳን ክፍሎች ወደ ሃያ የሚሆኑ ስጦታዎች ተዘርዝረው እንመለከታለን፡፡
ስጦታን እንዴት ማወቅ ይቻላል
እግዚአብሔር ስጦታ ሰጥቶኛል? ስጦታዬስ ምንድነው? የተፈጥሮ ችሎታዬን የእግዚአብሔር ስጦታ ነው ማለት እችላለሁ? ስጦታ ያድጋል አያድግም? … ሌሎች ሌሎች ጥያቄዎች ይኖሩን ይሆናል። ረጋ ብለን እያስተዋልን እግዚአብሔር መልስ ይሰጣል።
እያንዳንዱ ክርስቲያን አንድ ወይም ከዚያ የበለጠ ስጦታ አለው
በጌታ ኢየሱስ ስም ተጠምቀው ዳግም የተወለዱ፣ በክርስቶስ ደም በተዋጀው ቤተሰብ ውስጥ እያንዳንዱ በእግዚአብሔር ቃል የተወለደ ልጅ ስጦታ ተቀብሏል። “ልዩ ልዩን የእግዚአብሔርን ጸጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደ መሆናችሁ እያንዳንዳችሁ እያሳስበናል (1ኛጴጥ. 410)። እያንዳንዱ ክርስቲያን ስጦታውን የማወቅና የማሳደግ ኃላፊነት አለበት። ልክ እንደ ዘር ወይም አዲስ እንደ ተወለደ ሕጻን መንፈሳዊ ስጦታዎችም ከትንሹ ይጀምሩና በጥንቃቄ ከተያዙ ያድጋሉ። በፍቅርና በእግዚአብሔር መንፈስ በመመካት ሳናቋርጥ ከተጠቀምንባቸው ግባቸውን የሚመቱ ጠንካራ መሣሪያዎች ይሆናሉ። ስጦታውን ባሳደገ መጠን የእግዚአብሔር ባሪያ ራሱ ጠቃሚ ሰው መሆን ይጀምራል። ስጦታው ከተቀባዩ አኳኋን፣ ባሕርይና ካለፈበት ልምምድ ጋር ይስማማል። ስጦታው የወደ ፊት ኑሮውን እንኳ ሊወስን ይችላል። ምክንያቱም ስጦታዎቹ የእግዚአብሔር መንፈስ እያንዳንዱ ክርስቲያን በሕይወት ዘመኑ ሊፈጽማቸው የሚገባቸውን ሥራዎች የሚያሳዩ ጠቋሚዎች ስለሆኑ ነው። ስጦታ ላንተ በግልህ የሚያስደስትህና ስሜት የሚያሳድርብህ የራስህ ስጦታ ምን ምን መሆኑን ለይተህ ስታውቅ ነው። ስጦታህን ለማወቅ ከሚረዱህ ነገሮች አራት ያህል እንጠቅሳለን።
በተፈጥሮ ችሎታህ ጀምር፣ በዚያ ግን አትቁም
የተፈጥሮ ችሎታና መንፈሳዊ ስጦታ አንድ ባይሆኑም እንኳ የተያያዙ ነገሮች ናቸው። እንድ ሰው እንዳለው ስጦታዎቹ “… በውስጥ የተደበቀ የተፈጥሮ ችሎታን ይጠቁማሉ”። እንግዲህ ስጦታን ለማወቅ ከሚደረጉ የመጀመሪያ እርምጃዎች አንዱ የተፈጥሮ ችሎታን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መጠቀም መጀመር ነው። እንግዲህ የመንፈሳዊ ስጦታን አንድ መለኪያ በጸሎት ማወቅ ይቻላል ። በእምነት ላይ በተመሠረተ ጽኑ ጸሎት አንጻር ማየት እንችላለን። ይኸም ጸሎት እግዚአብሔር የሚያስፈልገንን እንዲሰጠን አንዴ ጠይቀነው የጠየቅነውን ነገር ለማግኘት በትዕግስት የምንጠባበቅበት ጸሎት መሆኑን የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል።
የተፈጥሮ ችሎታን በሥራ ላይ ስናውል በውጤቱ አንድ ከተፈጥሮ ውጪ (መንፈሳዊ) የሆነ ለውጥ በሰው ላይ መምጣቱ ነው። ይህም ማለት ሰዎች ወደ ጌታ ኢየሱስ ሲሳቡ ወይም በእምነታቸው ሲታነጹ ነው። ይህ መታነጽ ያለ መንፈስ ቅዱስ አይመጣም። ሆኖም አንድ ሰው የተፈጥሮ ችሎታ ኖሮት ከዚህ ጋር የተያያዘ መንፈሳዊ ስጦታ ላይኖረው ይችላል። ለምሳሌ ስድስት ዘማሪዎች ሁሉም በሙዚቃ ችሎታቸው እኩል የሆኑ በተለያዩ ጊዜአት ይዘምራሉ። አድማጮችም በሰሙት ሙዚቃ በጣም እንደ ተደሰቱ በማድነቅ ይናገራሉ። ነገር ግን ከስድስቱ አንዱ ከተፈጥሮ ችሎታው ጋር መንፈሳዊ ስጦታም አለው። እሱ ሲዘምር የእግዚአብሔር ህልውና በአዲስ መንገድ ይከሰታል። ሰዎች ወደ ጌታ ኢየሱስ ይጠጋሉ። የእግዚአብሔር መንፈስ በመዝሙሩ ቃላት ውስጥ ለሕይወታቸው የሚያስፈልገውን መልእክት ያስተላልፋል። ብቻ … አንድ መለኰታዊ ነገር ይፈጸማል። እኩል የተፈጥሮ ችሎታ ካላቸው ከሌሎቹ ከአምስቱ በተለየ ሁኔታ ያ አንድ ዘማሪ መንፈሳዊ ስጦታውን በሥራ ላይ እያዋለ ነው።
አንዳንድ መንፈሳዊ ስጦታዎች “ከተሰወሩ” የተፈጥሮ ችሎታዎች ጋር የተያያዙ ናቸው።
ቤተክርስቲያን የምትልህን አድምጥ
ሌሎች ከአዲስ አንጻር ያዩናል። እኛ ራሳችንን ከምናውቀው በተለየ መንገድ ያውቁናል። በግል መለኪያችን ብቻ ራሳችንን ከመዘንን ስለ ራሳችን የማናውቃቸውን ድብቅ ነገሮች ሳናስተውል እንቀራለን። የተቀበልነውን ስጦታ እንድናስተውል ሌሎች ሊረዱን ይችላሉ። ስጦታህን ለማወቅ እንዲረዱህ ባለህ ስጦታ መትጋት ጥሩ ነው። ጊዜ ወስዶ ከመጋቢና ከሌሎች አገልጋዮች ጋር መጸለይ መልካም ነው። ይህ አንዱ የሌላውን ስጦታ በመግለጽ እንዲተባበር ሊረዳ ይችላል። ይህ መንገድ ስለ እግዚአብሔር ስጦታዎች በቂ የሆነ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አመለካከት ሲኖርበት ግቡን ይመታል። የእግዚአብሔር ሕዝብ ኅብረት በሌላም መንገድ ሊጠቅመን ይችላል። የቤተ ክርስቲያን አባሎች ወይም መሪዎች አንዳንድ ኃላፊነቶችን እንድንቀበል ወይም የተለያዩ ሥራዎችን እንድንፈጽም ሊጠይቁን ይችላሉ። የወጣት መክሊት አገልግሎት ውስጥ እንድናገለግል ፣የሰንበት ትምህርት እንድናስተምር ከተጠየቅን ምናልባት የማስተማር ስጦታ ኖሮን ይሆናል። በቤተ ክርስቲያን ባሉ አገልግሎት ውስጥ ሥራ ቢሰጠን ከብዙ ስጦታዎች አንዱን ሊጠቁመን ይችላል፤ ማበረታታት፣ እርዳታን ማድረግ፣ አስተዳደርን ወይም ሌላ ስጦታን።
አንድ ሰው ያለ መንፈሳዊ ስጦታ የማስተማርን አገልግሎት ጀምሮ ይሆናል። ሌላው ደግሞ ያለ ስጦታው በኰሚቴ ውስጥ ሊያገለግል ይችላል። ግን ምንም ያህል የሚያበረክቱት ጠቃሚ ነገር አይኖርም። አገልግሎት ቢኖረንም መንፈሳዊ ስጦታ እለን ማለት ማረጋገጫ አይሆንም። ይህ የሚያሳየን ሥራውን እንድናደርግ ዕድል እንደ ተሰጠን ብቻ ነው። ክርስቲያን በተሰጠው አገልግሎት ውስጥ ምንም መንፈሳዊ ስጦታ ካላየበት የአገልግሎቱ ጊዜ እስኪያልቅ ጠብቆ ወደ ሌላ አገልግሎት ቢዛወር ይሻላል። ስጦታን ማሳደግ ብዙ ጥረትና መውደቅና መነሳት የሚጠይቅ ሥራ ነው። ነገር ግን ሰው ከሾመን ሹመት ይልቅ እግዚአብሔር የሰጠን አገልግሎት ይበልጣል። ስለዚህ ከላይ በቃሉ ላይ እንዳየነው ትሁት በመሆን ጸጋውን እንዲሰጠን መለመን አለብን፡፡
በመውደቅ በመነሳት ተማር
ስጦታህ በሌሎች ላይ ያመጣውን ለውጥ ለማስተዋል ሞክር። ምን እንደሚሰማቸው ለማወቅ ሞክር። እግዚአብሔር ያንን ችሎታ ሌሎችን ከመውደቃቸው ለማንሳት እየደጋገመ ከተጠቀመበት ምናልባት እሱ ስጦታህ ይሆናል።
ስታገለግል በሚሰጥህ እርካታ ስጦታህን ለማወቅ ሞክር
መንፈሳዊ ስጦታህን በቤተ ክርስቲያን ክልል ብቻ አትወስነው። እግዚአብሔር የሚሰጥህ ማንኛውም የሥራ ስሜት ለመንፈሳዊ ስጦታ ፍንጭ እንደሆኑ ለማየት ሞክር። ለምሳሌ አንድ ሰው በእጅ የሚሠራ ነገር ማድረግ ይወዳል። መኪና መጠገን፣ የተሰባበሩ ነገሮችን ማስተካከል…፤ ይህ ሰው ከዚህም ሌላ ከሰዎች ጋር መሥራት በጣም ይወዳል እንበል። ከተፈጥሮ ችሎታው ጋር የመርዳት ስጦታም አለው ማለት ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 1228)። ከዚህ የተነሳ ሰዎች እንዲረዳቸው ሁልጊዜ ይጠሩታል። ይህም የመርዳት አገልግሎት ጌታ ኢየሱስን ከማስከበሩም ሌላ ይህንን ወንድም በጣም ያረካዋል። አስተውል፦ መንፈሳዊ ስጦታን መጠቀም ደስታንና እርካታን ያመጣል። እርግጥ አንዳንዶቹ ይህንን ደስታና እርካታ በሙላት ላያገኙ ይችላሉ ይህ የሚሆነው የእግዚአብሔርን መንፈስ ስለሚያሳዝኑ ነው። ስጦታ ከእግዚአብሔር ቢሰጥም ተቀባዩ ለራሱ ክብር ሲያደርገው ሊያበላሸው ይችላል። ነገር ግን የአካሉ ራስ ከሆነው ከክርስቶስ ጋር ትክክለኛ ግንኙነት ሲኖር የአካሉ ብልቶች ሁሉ በስጦታው ይደሰታሉ።
ስጦታችንን ለማወቅ በምናደርገው ጥረት የውድድር መንፈስ ጨርሶ መወገድ አለበት። ከሌሎች ጋር ራሳችንን ማስተያየትም ሆነ ማወዳደር ፍጹም አልተፈቀደም። ይህን ማድረግ ሁሉም ቻይና ሁሉን አዋቂ የሆነውንና ስጦታውንም የሚሰጠውን እግዚአብሔርን አለማክበር ነው። ከዚህ ይልቅ ሌሎች ስጦታቸውን እንዲለዩ ያንተንም እንዲያሳዩህ እርዳቸው። በስጦታቸው መደሰትንና መጠቀምን ተማር። ስለነርሱ እግዚአብሔርን አመስግን። በሌሎች ስጦታ መደሰት ስለ ሌሎች ያለንን መጥፎ አስተያየት ለማስወገድ የክርስቶስን አካል አንድነት ለመጠበቅና ለመረዳዳት ይጠቅማል። መንፈሳዊ ስጦታዎች በፍቅር ካልተሠራባቸው ምንም አይጠቅሙም (1ኛ ቆሮንቶስ 13)። ፍቅር የጐደለውን ይሞላል። ያለመረዳትንና ውድቀትን ያስወግዳል። ፍቅር ይቅርታ ያደርጋል፤ ያማክራል፤ ያስተካክላል። ፍቅር የመንፈስ ስጦታዎችን ማሰናከያዎች ሳይሆኑ ማስተካከያዎች ያደርጋቸዋል። ደስ የሚልና ጠቃሚ ሕይወት እንዲኖርህ መንፈሳዊ ስጦታዎችህን እወቅ። በክርስቶስ አካል ውስጥ ያለህን የአገልግሎት ድርሻ አሳድግ። ለሌሎች መታነጽ ስጦታህን በፍቅር ለመጠቀም በሙሉ ኃይልህ ሥራ። “ልዩ ልዩ የእግዚአብሔርን ጸጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደ መሆናችሁ እያንዳንዳችሁ የጸጋን ስጦታ እንደ ተቀበላችሁ መጠን በዚያው ጸጋ እርስ በርሳችሁ አገልግሉ።”
ግንኙነታቸው
1ኛ. የሁለቱም ምንጭ እግዚአብሔር መሆኑ፣ እግዚአብሔር በተፈጥሮአችን ውስጥ ለተቀመጡ ልዩ ልዩ ችሎታዎቻችን ምንጭ ነው፡፡ ማንም ለራሱ ያንን ማድረግ አይቻለውም፡፡ ተፈጥሮአዊ ችሎታዎቻችን በስልጠና ቢዳብሩም በምርጫችን የኛ ልናደርጋቸው አንችልም፡፡ ድምጻችንን፣ በባሕሪያችን ውስጥ የተቀመጡ ልዩ ልዩ የማንነቶቻችን መግለጫዎች የመነጩት ከሰጪው ነው፡፡
2ኛ. ተፈጥሮአዊ ችሎታዎች ለበጎ ምግባር የሚውሉ መሆናቸው፣ በተፈጥሮ ችሎታችን ውስጥ የተቀመጡ አንዳንድ ተሰጥኦዎች እግዚአብሔር በአማኙ ውስጥ ለሚሠራው ሥራ አመቺ ሁኔታን ይፈጥራሉ፡፡ ለምሳሌ ድምጻቸው መረዋ የሆኑ ሰዎች ዘፋኝ ሆነው ያገለገሉትን ያህል ዘማሪ ሆነው ሊያገልገሉ የሚችሉበት ሁኔታ መፈጠሩ፣ በባህሪያቸው ለጋስ የሆኑ ሰዎች የምህረት አድራጊነት ጸጋ በውስጣቸው ሊሠራ መቻሉ፣ ተናጋሪና ፀሐፊ የሆኑ ሰዎችን ሰባኪና መምህራን ለመሆን መቻላቸው ከብዙ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ፡፡
መንፈሳዊ ስጦታዎች
የጸጋ ስጦታዎች ስማቸው እንደሚያመለክተው እግዚአብሔር ከርህራሄው የተነሳ ቅጣት ለሚገባቸው ሰዎች ያደረገው ልግስናዎች ናቸው፡፡ ሁሉም አማኞች የዚህ እድል ፈንታ ተካፋይ ናቸው፡፡
ይሁን እንጂ ስጦታውን የሚቀበሉና በአግባቡ የሚያስተናግዱ ብዙ አይደሉም፡፡ መንፈሳዊ ስጦታዎች ለተቀባዩ ጥቅምና መታነጽ የተሰጡ ቢሆንም አውራ ግባቸው የክርስቶስን አካል ማነቃቃትና መገንባት ነው፡፡ ስለ ስጦታ በተጠቀሰባቸው አራቱ የአዲስ ኪዳን ክፍሎች ወደ ሃያ የሚሆኑ ስጦታዎች ተዘርዝረው እንመለከታለን፡፡
ስጦታን እንዴት ማወቅ ይቻላል
እግዚአብሔር ስጦታ ሰጥቶኛል? ስጦታዬስ ምንድነው? የተፈጥሮ ችሎታዬን የእግዚአብሔር ስጦታ ነው ማለት እችላለሁ? ስጦታ ያድጋል አያድግም? … ሌሎች ሌሎች ጥያቄዎች ይኖሩን ይሆናል። ረጋ ብለን እያስተዋልን እግዚአብሔር መልስ ይሰጣል።
እያንዳንዱ ክርስቲያን አንድ ወይም ከዚያ የበለጠ ስጦታ አለው
በጌታ ኢየሱስ ስም ተጠምቀው ዳግም የተወለዱ፣ በክርስቶስ ደም በተዋጀው ቤተሰብ ውስጥ እያንዳንዱ በእግዚአብሔር ቃል የተወለደ ልጅ ስጦታ ተቀብሏል። “ልዩ ልዩን የእግዚአብሔርን ጸጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደ መሆናችሁ እያንዳንዳችሁ እያሳስበናል (1ኛጴጥ. 410)። እያንዳንዱ ክርስቲያን ስጦታውን የማወቅና የማሳደግ ኃላፊነት አለበት። ልክ እንደ ዘር ወይም አዲስ እንደ ተወለደ ሕጻን መንፈሳዊ ስጦታዎችም ከትንሹ ይጀምሩና በጥንቃቄ ከተያዙ ያድጋሉ። በፍቅርና በእግዚአብሔር መንፈስ በመመካት ሳናቋርጥ ከተጠቀምንባቸው ግባቸውን የሚመቱ ጠንካራ መሣሪያዎች ይሆናሉ። ስጦታውን ባሳደገ መጠን የእግዚአብሔር ባሪያ ራሱ ጠቃሚ ሰው መሆን ይጀምራል። ስጦታው ከተቀባዩ አኳኋን፣ ባሕርይና ካለፈበት ልምምድ ጋር ይስማማል። ስጦታው የወደ ፊት ኑሮውን እንኳ ሊወስን ይችላል። ምክንያቱም ስጦታዎቹ የእግዚአብሔር መንፈስ እያንዳንዱ ክርስቲያን በሕይወት ዘመኑ ሊፈጽማቸው የሚገባቸውን ሥራዎች የሚያሳዩ ጠቋሚዎች ስለሆኑ ነው። ስጦታ ላንተ በግልህ የሚያስደስትህና ስሜት የሚያሳድርብህ የራስህ ስጦታ ምን ምን መሆኑን ለይተህ ስታውቅ ነው። ስጦታህን ለማወቅ ከሚረዱህ ነገሮች አራት ያህል እንጠቅሳለን።
በተፈጥሮ ችሎታህ ጀምር፣ በዚያ ግን አትቁም
የተፈጥሮ ችሎታና መንፈሳዊ ስጦታ አንድ ባይሆኑም እንኳ የተያያዙ ነገሮች ናቸው። እንድ ሰው እንዳለው ስጦታዎቹ “… በውስጥ የተደበቀ የተፈጥሮ ችሎታን ይጠቁማሉ”። እንግዲህ ስጦታን ለማወቅ ከሚደረጉ የመጀመሪያ እርምጃዎች አንዱ የተፈጥሮ ችሎታን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መጠቀም መጀመር ነው። እንግዲህ የመንፈሳዊ ስጦታን አንድ መለኪያ በጸሎት ማወቅ ይቻላል ። በእምነት ላይ በተመሠረተ ጽኑ ጸሎት አንጻር ማየት እንችላለን። ይኸም ጸሎት እግዚአብሔር የሚያስፈልገንን እንዲሰጠን አንዴ ጠይቀነው የጠየቅነውን ነገር ለማግኘት በትዕግስት የምንጠባበቅበት ጸሎት መሆኑን የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል።
የተፈጥሮ ችሎታን በሥራ ላይ ስናውል በውጤቱ አንድ ከተፈጥሮ ውጪ (መንፈሳዊ) የሆነ ለውጥ በሰው ላይ መምጣቱ ነው። ይህም ማለት ሰዎች ወደ ጌታ ኢየሱስ ሲሳቡ ወይም በእምነታቸው ሲታነጹ ነው። ይህ መታነጽ ያለ መንፈስ ቅዱስ አይመጣም። ሆኖም አንድ ሰው የተፈጥሮ ችሎታ ኖሮት ከዚህ ጋር የተያያዘ መንፈሳዊ ስጦታ ላይኖረው ይችላል። ለምሳሌ ስድስት ዘማሪዎች ሁሉም በሙዚቃ ችሎታቸው እኩል የሆኑ በተለያዩ ጊዜአት ይዘምራሉ። አድማጮችም በሰሙት ሙዚቃ በጣም እንደ ተደሰቱ በማድነቅ ይናገራሉ። ነገር ግን ከስድስቱ አንዱ ከተፈጥሮ ችሎታው ጋር መንፈሳዊ ስጦታም አለው። እሱ ሲዘምር የእግዚአብሔር ህልውና በአዲስ መንገድ ይከሰታል። ሰዎች ወደ ጌታ ኢየሱስ ይጠጋሉ። የእግዚአብሔር መንፈስ በመዝሙሩ ቃላት ውስጥ ለሕይወታቸው የሚያስፈልገውን መልእክት ያስተላልፋል። ብቻ … አንድ መለኰታዊ ነገር ይፈጸማል። እኩል የተፈጥሮ ችሎታ ካላቸው ከሌሎቹ ከአምስቱ በተለየ ሁኔታ ያ አንድ ዘማሪ መንፈሳዊ ስጦታውን በሥራ ላይ እያዋለ ነው።
አንዳንድ መንፈሳዊ ስጦታዎች “ከተሰወሩ” የተፈጥሮ ችሎታዎች ጋር የተያያዙ ናቸው።
ቤተክርስቲያን የምትልህን አድምጥ
ሌሎች ከአዲስ አንጻር ያዩናል። እኛ ራሳችንን ከምናውቀው በተለየ መንገድ ያውቁናል። በግል መለኪያችን ብቻ ራሳችንን ከመዘንን ስለ ራሳችን የማናውቃቸውን ድብቅ ነገሮች ሳናስተውል እንቀራለን። የተቀበልነውን ስጦታ እንድናስተውል ሌሎች ሊረዱን ይችላሉ። ስጦታህን ለማወቅ እንዲረዱህ ባለህ ስጦታ መትጋት ጥሩ ነው። ጊዜ ወስዶ ከመጋቢና ከሌሎች አገልጋዮች ጋር መጸለይ መልካም ነው። ይህ አንዱ የሌላውን ስጦታ በመግለጽ እንዲተባበር ሊረዳ ይችላል። ይህ መንገድ ስለ እግዚአብሔር ስጦታዎች በቂ የሆነ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አመለካከት ሲኖርበት ግቡን ይመታል። የእግዚአብሔር ሕዝብ ኅብረት በሌላም መንገድ ሊጠቅመን ይችላል። የቤተ ክርስቲያን አባሎች ወይም መሪዎች አንዳንድ ኃላፊነቶችን እንድንቀበል ወይም የተለያዩ ሥራዎችን እንድንፈጽም ሊጠይቁን ይችላሉ። የወጣት መክሊት አገልግሎት ውስጥ እንድናገለግል ፣የሰንበት ትምህርት እንድናስተምር ከተጠየቅን ምናልባት የማስተማር ስጦታ ኖሮን ይሆናል። በቤተ ክርስቲያን ባሉ አገልግሎት ውስጥ ሥራ ቢሰጠን ከብዙ ስጦታዎች አንዱን ሊጠቁመን ይችላል፤ ማበረታታት፣ እርዳታን ማድረግ፣ አስተዳደርን ወይም ሌላ ስጦታን።
አንድ ሰው ያለ መንፈሳዊ ስጦታ የማስተማርን አገልግሎት ጀምሮ ይሆናል። ሌላው ደግሞ ያለ ስጦታው በኰሚቴ ውስጥ ሊያገለግል ይችላል። ግን ምንም ያህል የሚያበረክቱት ጠቃሚ ነገር አይኖርም። አገልግሎት ቢኖረንም መንፈሳዊ ስጦታ እለን ማለት ማረጋገጫ አይሆንም። ይህ የሚያሳየን ሥራውን እንድናደርግ ዕድል እንደ ተሰጠን ብቻ ነው። ክርስቲያን በተሰጠው አገልግሎት ውስጥ ምንም መንፈሳዊ ስጦታ ካላየበት የአገልግሎቱ ጊዜ እስኪያልቅ ጠብቆ ወደ ሌላ አገልግሎት ቢዛወር ይሻላል። ስጦታን ማሳደግ ብዙ ጥረትና መውደቅና መነሳት የሚጠይቅ ሥራ ነው። ነገር ግን ሰው ከሾመን ሹመት ይልቅ እግዚአብሔር የሰጠን አገልግሎት ይበልጣል። ስለዚህ ከላይ በቃሉ ላይ እንዳየነው ትሁት በመሆን ጸጋውን እንዲሰጠን መለመን አለብን፡፡
በመውደቅ በመነሳት ተማር
ስጦታህ በሌሎች ላይ ያመጣውን ለውጥ ለማስተዋል ሞክር። ምን እንደሚሰማቸው ለማወቅ ሞክር። እግዚአብሔር ያንን ችሎታ ሌሎችን ከመውደቃቸው ለማንሳት እየደጋገመ ከተጠቀመበት ምናልባት እሱ ስጦታህ ይሆናል።
ስታገለግል በሚሰጥህ እርካታ ስጦታህን ለማወቅ ሞክር
መንፈሳዊ ስጦታህን በቤተ ክርስቲያን ክልል ብቻ አትወስነው። እግዚአብሔር የሚሰጥህ ማንኛውም የሥራ ስሜት ለመንፈሳዊ ስጦታ ፍንጭ እንደሆኑ ለማየት ሞክር። ለምሳሌ አንድ ሰው በእጅ የሚሠራ ነገር ማድረግ ይወዳል። መኪና መጠገን፣ የተሰባበሩ ነገሮችን ማስተካከል…፤ ይህ ሰው ከዚህም ሌላ ከሰዎች ጋር መሥራት በጣም ይወዳል እንበል። ከተፈጥሮ ችሎታው ጋር የመርዳት ስጦታም አለው ማለት ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 1228)። ከዚህ የተነሳ ሰዎች እንዲረዳቸው ሁልጊዜ ይጠሩታል። ይህም የመርዳት አገልግሎት ጌታ ኢየሱስን ከማስከበሩም ሌላ ይህንን ወንድም በጣም ያረካዋል። አስተውል፦ መንፈሳዊ ስጦታን መጠቀም ደስታንና እርካታን ያመጣል። እርግጥ አንዳንዶቹ ይህንን ደስታና እርካታ በሙላት ላያገኙ ይችላሉ ይህ የሚሆነው የእግዚአብሔርን መንፈስ ስለሚያሳዝኑ ነው። ስጦታ ከእግዚአብሔር ቢሰጥም ተቀባዩ ለራሱ ክብር ሲያደርገው ሊያበላሸው ይችላል። ነገር ግን የአካሉ ራስ ከሆነው ከክርስቶስ ጋር ትክክለኛ ግንኙነት ሲኖር የአካሉ ብልቶች ሁሉ በስጦታው ይደሰታሉ።
ስጦታችንን ለማወቅ በምናደርገው ጥረት የውድድር መንፈስ ጨርሶ መወገድ አለበት። ከሌሎች ጋር ራሳችንን ማስተያየትም ሆነ ማወዳደር ፍጹም አልተፈቀደም። ይህን ማድረግ ሁሉም ቻይና ሁሉን አዋቂ የሆነውንና ስጦታውንም የሚሰጠውን እግዚአብሔርን አለማክበር ነው። ከዚህ ይልቅ ሌሎች ስጦታቸውን እንዲለዩ ያንተንም እንዲያሳዩህ እርዳቸው። በስጦታቸው መደሰትንና መጠቀምን ተማር። ስለነርሱ እግዚአብሔርን አመስግን። በሌሎች ስጦታ መደሰት ስለ ሌሎች ያለንን መጥፎ አስተያየት ለማስወገድ የክርስቶስን አካል አንድነት ለመጠበቅና ለመረዳዳት ይጠቅማል። መንፈሳዊ ስጦታዎች በፍቅር ካልተሠራባቸው ምንም አይጠቅሙም (1ኛ ቆሮንቶስ 13)። ፍቅር የጐደለውን ይሞላል። ያለመረዳትንና ውድቀትን ያስወግዳል። ፍቅር ይቅርታ ያደርጋል፤ ያማክራል፤ ያስተካክላል። ፍቅር የመንፈስ ስጦታዎችን ማሰናከያዎች ሳይሆኑ ማስተካከያዎች ያደርጋቸዋል። ደስ የሚልና ጠቃሚ ሕይወት እንዲኖርህ መንፈሳዊ ስጦታዎችህን እወቅ። በክርስቶስ አካል ውስጥ ያለህን የአገልግሎት ድርሻ አሳድግ። ለሌሎች መታነጽ ስጦታህን በፍቅር ለመጠቀም በሙሉ ኃይልህ ሥራ። “ልዩ ልዩ የእግዚአብሔርን ጸጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደ መሆናችሁ እያንዳንዳችሁ የጸጋን ስጦታ እንደ ተቀበላችሁ መጠን በዚያው ጸጋ እርስ በርሳችሁ አገልግሉ።”