እምነት /FAITH IN GOD/
ከመሠረታዊ የክርስቲያን ትምህርቶች አንዱና ዋነኛዉ እምነት ነዉ፡፡ እግዚአብሔር ያዘጋጀልልን ደህንነትም ሆነ ከደህንነት ቀጥሎ ልንቀበላቸዉ ያሉ በረከቶች ሁሉ፣ እንዲሁም መለኮታዊ ባህሪያትን ሁሉ መካፈል የምንችለዉ በእምነት ነዉ (2ኛጴጥ. 1፡5-11) ፡፡
በክርስትና ሕይወታችን ስኬታማ ለመሆንም እምነት ያስፈልገናል፣ የጻድቅ መኖሪያዉ እምነት ነዉና (ሮሜ1፡17) ፡፡ያለእምነትም የሆነ ነገር ሁሉ ኃጢያት ነዉ (ሮሜ.14፡23) ፡፡
8.1. እምነት ያልሆኑ ነገሮች
እምነት ስንል የሚከተሉትን ማለታችን አይደለም ፡፡
ሀ. እምነት ኃይማኖት (Religion) አይደለም ፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ‹‹እኛ የራሳችን እምነት አለን ››ሲሉ ይደመጣሉ ፡፡
ለ. እምነት ከአእምሮ ጋር መስማማት አይደለም ፡፡እምነት በአእምሮ ስሜት ላይ የሚደገፍ የአእምሮ ቀመር አይደለም ፡፡ ብዙ ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነና እዉነትም እንደሆነ፣ እንደሚያምኑም ይናገራሉ ፡፡ ነገር ግን ይህ አይነቱ እምነት ህይወታቸዉንና ኑሮአቸዉን የማይቀይር ነዉ (ያዕ 2፡14) ፡፡ ይህ አይነቱ እምነት አጋንንትም ያላቸዉ የእምነት አይነት ነዉ (ያዕ.2፡19)
ሐ. እምነት እግዚአብሔርን እንደፈለግን የምናንቀሳቅስበት እና በግላዊ ምቾታችን ላይ የተደገፈ አይደለም፡፡
መ. እምነት ተስፋም፣ መልካም መሻትም አይደለም፡፡ ተስፋ መልካም ነዉ፡፡ በትእግስትም የወደፊቱን መጠበቅ ያስችለናል ፡፡ ይሁን እንጂ እምነት ተስፋን አሁን እንዳገኘ ይቀበላል፡፡
ተስፋ የአእምሮ (የነፍስ) ሲሆን (1ተሰ.5፡8፣ ዕብ.6፡19) የነፍስ መልህቅ ነዉ፡፡ ተስፋ ልናምን በምንችልበት ስፍራ ላይ አጽንቶ ያቆመናል እንጂ ግን ያለ ተስፋ እምነት የለም፡፡
በእግዚአብሔር እምነት ሁልጊዜ በልብ ነዉ (ሮሜ. 10፡10) ፡፡
8.2. እምነት ምንድን ነዉ?
መጽሐፍ ቅዱስ እምነትን በዕብ. 11፡1 እንደሚተረጉመዉ፡-
ሀ. እምነት ማለት እግዚአብሔር የተናገረዉን ተስፋ ሁሉ እንደፈጸመዉ እርግጠኛ ሆኖ መረዳት ነዉ (The dictionary describes faith as a complete trust and confidence, firm belief without
logical proof) ፡፡
ለ. እምነት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከንን መቀበል መቻል ነዉ (ኤፌ.1፡3) ፡፡
ሐ. እምነት ተስፋዎቻችን ሁሉ እንደተቀበልን የሚያረጋግጥ በእጃችን (በልባችን) ያለ ቼክ ነዉ፡፡ (1ዩሐ. 5፡14-15፣ ማር.11፡23-24) ፡፡
መ. እምነት እግዚአብሔር የተናገራቸዉ ቃሎች ላይ ተመስርቶ የሌለዉን ማለትም በስጋ አይን ያላየነዉን እንዳለ አድርጎ መጥራት መቻል ነዉ፡፡ ይህም ማለት ነገሮች በእግዚአብሔር እንደሆኑ ማየት እንጂ በተፈጥሮ እይታ አንጻር የሚመስሉትን ማየት አይደለም (ሮሜ.4፡16-17) ፡፡ እግዚአብሔር በዘፍ.17፡5 ላይ ሲናገር የአሕዛብ አባት አደርግሃለሁ ሳይሆን አድርጌሃለሁ በማለት ነዉ፡፡ስለዚህ የእምነት አባት የሆነዉ አብርሃም በሚያደርገዉ ሁሉ በእግዚአብሔር እምነት ነበረዉ፡፡
• በአለማመን አልተጠራጠረም ፡፡
• ተስፋ የሰጠዉ እግዚአብሔር የታመነ እንደሆነ ቆጠረ ፡፡
• በእግዚአብሔር ቃል ላይ የሚቃረንን ማንኛዉንም የተፈጥሮ መረጃዎችን አልተቀበለም (ዕብ.11፡8-12፣ሮሜ. 4=16-22) ፡፡
8.3. እምነትን እንዴት እናገኛለን?
ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት እንደማንችል የተናገረዉ እርሱ እምነትንም ማግኘት የምንችልበትንም መንገድ ነግሮናል፡፡ እምነት የሌለን ከሆንን ተጠያቂ ልናደርገዉ የምንችለዉ የራሳችንን አለማወቅ እንጂ እግዚአብሔርን ሊሆን አይችለም ፡፡
እምነት የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ይመጣል (ሮሜ.10፡17) ፡፡ ከዚህ አንጻር እምነት የእግዚአብሔር ስጦታ እንደሆነ እንመለከታለን ፡፡ ‹‹ፀጋዉ በእምነት አድኗቸዋልና ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነዉ እንጂ ከእናንተ አይደለም ማንም እንዳይመካ ከስራ አይደለም (ኤፌ.2፡8) ፡፡
የእግዚአበሔር ቃል በራሱ የእምነት ቃል እንደሆነ መጽሐፍ ይናገራል፡፡ እምነትም የሚገኘዉ ይህንኑ የእምነት ቃል ከመስማት ነዉ (ሮሜ. 10=8፣14፣17) ፡፡
• ቆርነሊዎስና ቤተሰቡ መዳንን ለማግኘት የሚያስችላቸዉን እምነት በመስማት አገኙ (ዮሐ.10፡5-6፣ 11፡13)፡፡
• በልስጥራንም እግሩ የሰለለዉ ሰዉ ጳዉሎስ የእግዚአብሔርን ቃል ሲናገር ሰምቶ እንዳመነና እንደተፈወሰ (የሐ.14፡8-10)፡፡
• ከ12 ዓመትም ጀምሮ ደም የሚፈሳት ሴት የኢየሱስን ወሬ ሰምታ ተፈዉሳለች (ማር.5፡25-34)፡፡
• የእግዚአብሔርን ቃል ዘወትር ሰምተን በልባችን እንድንጠብቀዉና የሚጠቅመን እንዲሆን የእግዚአብሔር ቃል ያሳሰበናል (ምሳ.4፡20-22) ፡፡
8.4. እምነትን ማሳደግ
እምነት ልክና መጠን አለዉ (ሮሜ.12፡3-6)
• እምነት በስናፍጭ ቅንጣት ተመጥኗል
• እምነት ያድጋልም ‹‹ስለ እምነታችሁ ማነስ ነዉ›› ይላልና፡፡
እምነትን ልናሳድግበት የምንችልባቸዉን መንገዶች እንደሚከተለዉ ልናይ እንችላለን፡-
ሀ. ዘወትር የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ፣ መማርና መስማት (ምሳ. 4፡20-22) ፡፡
ለ. ዘወትር በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና በመንፈስ ቅዱስም መጸለይ (ይሁዳ 20፣1ቆሮ.14፡4) የመንፈስ ፍሬ ተብለዉ ከተጠቀሱት ዉስጥ አንዱ እምነት ነዉ፡፡
ሐ. ዘወትር በምንሰማዉ የእግዚአብሔር ቃል መሰረት ተግባራዊ ርምጃዎችን በየደረጃዉ መዉሰድን መለማመድ፡፡ እግዚአብሔር በገለጠልን በጥቂቷ ነገር ታማኝ በመሆን ካልተገበርነዉ የበለጠዉን ነገር እግዚአብሔር አይገለጥልንም ፡፡
መ. የኑሮአቸዉን ፍሬ በመመልከት በእምነታቸዉ መምሰል ይቻል ዘንድ በተቻለ መጠን ሁሉ ከእምነት ሰዎች ጋር ጊዜን ማሳለፍ (ዕብ.13፡7፣ ምሳ.13፡20) ፡፡
ሠ. የእግዚአብሔር ቃል እንደሚያስተምረን እምነት የሚሰራዉ በፍቅር ነዉ (ገላ.5፡6) ፡፡ ለምሳሌ ያህል የመቶ አለቃዉ (ማቴ.8፡5-13) እና ከነናዊቷ ሴት (ማቴ.15፡21-28) ወደ ኢየሱስ እንዲቀርቡ ያነሳሳቸዉ ጉዳይ ፍቅር ነበር ፡፡ ሁለቱም ታላቅ እምነት የነበራቸዉ እንደነበሩ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስረድቷል፡፡
ረ. የእምነት ምስክርነትን (confession) መጠበቅ (ዕብ. 10፡23፣ ሮሜ.10፡10፣ ኢያ.1፡8) ፡፡
ሰ. ዘወትር ቅድስናን መፈለግ (ዕብ.12፡14) ፡፡ የልብ ንጽህናና የይቅርታ ልብ ከሌለ የልብ እምነት እንዳይኖር አስተዋጾ ስላለዉ ነው፡፡
8.5. የእምነት ገጽታዎች
የዕብራዊያን መልእክት ምእራፍ 11‹‹የእምነት ምእራፍ›› በመባል ይታወቃል ፡፡ በምእራፍ ዉስጥ ሁለት የእምነት ገጽታዎች ተገልጸዋል፡፡ እነርሱም፡-
ሀ. የአሸናፊ ድል የመንሳት እምነት (victorious-overcomers) (1-35)
• ዳንኤል ከአንበሶች ጉድጓድ (ዳን.6)
• ሲድራቅ፣ ሚሳቅ እና አብድናጎ ከእቶኑ እሳት (ዳን.3)
• የባልቴቷ ልጅ ከሞት መነሳት (1ነገ.17)
• ዳዊት ከሰይፍ በተደጋጋሚ መዳኑ
ለ. በመከራ ጸንቶ የመታመን እምነት (faithfulness in suffering) (35-40)
• ኤርሚያስ በወህኒ (ኤር.37-38) ፤
• ኢሳያስ በመጋዝ ለሁለት ተሰንጥቆ ፤
• ሚኪያስ በጥፊ ሲመታ ፤
• ዘካርያስ እስከሞት በድንጋይ መወገር (2ዜና 24፣ማቴ23፡35-37) ፡፡
ስለዚህ እምነት ከመከራ ነጻነትን መቀበል፣ ከህመም መፈወስን እንዲሁም ለፍላጎታችን ሁሉ አቅራቦትን መቀበል ማለት ብቻ አይደለም ፡፡ እምነት እስራት በጸና ጊዜ፣ ጸሎታችን ተሰምቶ መልስ ያላገኘን በመሰለን ጊዜና ታእምራዊ አቅራቦቶችን ባላገኘን ጊዜም በመከራ ጸንቶ እግዚአብሔርን መታመን ነዉ፡፡ የቀደሙት የእምነት አባቶችም በምሳሌነታቸዉ የተመሰከረላቸዉ በነዚሁ በሁለቱም የእምነት ገጽታዎች ነበር (ዕብ. 11፡32-40) ፡፡
8.6. እምነት በአማኞች ህይወት እንዴት ሊገለጥ ይችላል?
እምነት በእግዚአብሔር ባህሪይ፣ ኃይልና በቃሉ ላይ የጸና መታመንን ይዞ አካሄዳችንን (ድርጊቶቻችንን) ከእርሱ ጋር በማድረግ ነዉ፡፡ ከዚህ አንጻር እምነት የሚገለጥባቸዉ መንገዶች የሚከተሉት ናቸዉ፡፡
• በአፍ ምስክርነት (statement of faith) (ሮሜ. 1፡5፣ ያዕ.2 14-26)
• በእምነት በመመላለስና በመኖር (2ቆሮ. 5፡7፣ ሮሜ.1፡17፣ገላ.2፡20)
8.7. የእምነት አስፈላጊነት
እግዚአብሔርን ማመን ወይም በእግዚአብሔር እምነት ለምን ያስፈልገናል?
ሀ. ያለእምነት መዳን አይቻልም (ዩሐ.3፡36፣ ኤፌ.2፡8) ፡፡ እምነት የፈዉስ፣ የአርነት አገልግሎትም ቁልፍ ነገር ነዉ፡፡
ለ. ዕብ.11፡6 እንደሚለዉ ‹‹ያለእምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤›› እኛ ደግሞ የተፈጠርነዉ ለእርሱ ደስታ ነዉ (ራዕ.4፡11፣ መዝ.147፡11) ፡፡ እርሱን ደግሞ ደስ የማናሰኝ ከሆንን የተፈጠርንበትን ዓላማ ዘንግተናል ማለት ነዉ፡፡
ሐ. በእምነት ያልሆነ ሁሉ ኃጢያት ነዉ (ሮሜ 14፡23) ፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ኃጢያትን ይጠላል፡፡ እግዚአብሔርን ማመን ባልቻልን ጊዜ ሁሉ እርሱ ሀሰተኛ እንደሆነ፣ የሰጠዉንም ተስፋ እንደማይፈጽም እየቆጠርነዉ ነዉ ያለነው ማለት ነው (ዘፍ. 23፡19) ፡፡
መ. አለማመን ወደ አለመታዘዝ ይመራናል ፡፡ የእግዚአብሔር ተስፋዎች እንዲፈጸሙ መታዘዝ አስፈላጊነዉ፡፡ለተገለጠልን የእግዚአብሔር ፈቃድ አለመታዘዝ ደግሞ በእግዚአብሔር አይን አመጽ ነዉ ፡፡
ሠ. እምነት የጻድቅ መኖሪያ ነው (ሮሜ.1፡17)
ረ. ያለእምነት በዚህች አለም ላይ በአሸናፊነትና በድል መኖር አይቻልም ዮሐ.5፡4)
ሰ. ያለእምነት ደስተኛ ሆኖ መኖር አይቻልም (1ጴጥ.1፡8-9)
ሸ. መንፈስ ቅዱስን መቀበል የሚቻለዉ በእምነት ነዉ (ገላ.3፡2)
ቀ. መጽደቅም በእምነት እንጂ በስራ አይደለም (ገላ.2፡16)
በ. ያለእምነት መጸለይም አንችልም (ያዕ.1፡6) መልስንም ከጌታ ኢየሱስ አንቀበልም (ማቴ.21፡22፡6፡11) ስለዚህ እምነት ለቁሳቁስ አቅራቦቶቻችንም ቁልፍ ነዉ፡፡
ተ. ሰውም ለመጠመቅ መጀመሪያ ማመን አለበት (ማር 16፡16) በእግዚአብሔር እምነት የሌላቸዉ ሁሉ የግድ በሌላ በአንድ ነገር ያምናሉ ማለት ነዉ፡፡ በኃይማኖት ወግ፣ በሳይንስ መረዳት፣ በተፈጥሮ መረጃዎች፣ በማስሚዲያዎች ወይም በእነዚህ ሁሉ
ቅንብር ያምናል (ሮሜ.1፡22) ፡፡ በእርግጥም ሙሉ በሙሉ በእግዚአብሔር የማያምኑ ሁሉ በአንድ ስፍራ በዳቢሎስ አምነዉ ራሳቸዉን ያገኙታል ፡፡ ሰይጣን እንዳለ ባለማመን እንኳን እያለ ሰዉ ሰይጣን የሚለዉን ማመንም ይቻላል ማለት ነዉ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር በእርሱና በሚለን እንድናምን መፈለጉና መጠበቁ ጻድቅ ነዉ፡፡ እዉነትን ሊነግረን፣ ሊረዳንና ለህይወት ጥያቄዎቻችን
ሁሉ መልስን ሊሰጠን እርሱ የታመነ ነዉና፡፡
8.8. እምነትን በተግባር (በሥራ) ላይ ማዋል
መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን እዉነተኛ የተፈተነ እምነት ‹‹በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋዉ ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር›› እንደሆነ ነዉ (1ጴጥ.1፡7) ፡፡ ስለዚህ በእምነት ህይወታችን ላይ ሊመጡ የሚችሉ ፈተናዎች እንዳሉ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ እምነትን በተገቢዉ መንገድ በተግባር ላይ ለማዋል የምንችለዉ፡-
ሀ. በማንኛዉም ጉዳዮቻችን በተመለከተ በእግዚአብሔር ቃል ዉስጥ የተገባልልን ኪዳን /ተስፋ መያዝ (ፊልጵ.4፡19፣2ቆሮ.1፡20) ፤
ለ. ተስፋዉ /ከኪዳኑ ጋር የተያያዙትን ቅድመ ሁኔታዎችን መፈጸም/ (1ዮሐ.5 ፣ዘዳ፡28፡1-3፣15፣ሚል.3፡7-12 (10) ፣ ማር.11፡24-25)፤
ሐ. የተስፋ ቃሎቻችን አምነን መናገራችንን (confession) ባለማቋረጥ መቀጠል ፤
መ. የሰማነዉን ቃል አድራጊዎች መሆን (ያዕ.1፡22-23፣ ዮሐ.9፡7፣ያዕ.2፡20-24) ፤
ሠ. ያመነዉንና የያዝነዉን እምነት በተግባር መለማመድ (ማቴ.9፡20-22 ፣14፡25-29) ፤
ረ. በራስ ማስተዋል አለመደገፍ (ምሳ.3፡1-6፡1ጢሞ.1፡4-7፡620-21፣ 2ጢሞ. 2፡16-18፣
ሮሜ.14፡1፣ቆላ.2፡8)
ሰ. ሰው ሲጠመቅ ያመነውን በሥራ ገለጸው ማለት ነው፡፡
8.9. የእምነት ጠላቶችን ድል መንሳት
እምነት በአማኞች ሕይወት እንዳይሰራና እንዳያድግ ከሚያደርጉት የእምነት ጠላቶች ዋናዎቹን እንደሚከተለዉ እንመለከታለን፡-
ሀ. አለማወቅ፡- ማንም ሰዉ ያልሰማዉንና ያላወቀዉን ተስፋ/ኪዳን ከእግዚአብሔር ዘንድ ሳይኖረዉ እምነት ሊኖረዉ ወይም እምነቱ ሊዳብር አይችልም ፡፡ ለዚህ ደግሞ መፍትሄዉ የእግዚአብሔርን ቃል ማጥናትና ማሰላሰልን ይጠይቃል ፡፡
ለ. ፍርሃት፡- ፍርሃት ክፉና መጥፎ ነገር ይደርስብኛል ብሎ በእዉነት ዕውቀት ላይ ያልተመሰረተ አሉታዊ ስሜት ነዉ (fear= false
evidence appearing real) ፡፡ በእግዚአብሔር አባታዊ ጥበቃ እና ፍቅር ላይ መታመን ያስፈልጋል (1ዮሐ.4:18) ፡፡
በክርስትና ሕይወታችን ስኬታማ ለመሆንም እምነት ያስፈልገናል፣ የጻድቅ መኖሪያዉ እምነት ነዉና (ሮሜ1፡17) ፡፡ያለእምነትም የሆነ ነገር ሁሉ ኃጢያት ነዉ (ሮሜ.14፡23) ፡፡
8.1. እምነት ያልሆኑ ነገሮች
እምነት ስንል የሚከተሉትን ማለታችን አይደለም ፡፡
ሀ. እምነት ኃይማኖት (Religion) አይደለም ፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ‹‹እኛ የራሳችን እምነት አለን ››ሲሉ ይደመጣሉ ፡፡
ለ. እምነት ከአእምሮ ጋር መስማማት አይደለም ፡፡እምነት በአእምሮ ስሜት ላይ የሚደገፍ የአእምሮ ቀመር አይደለም ፡፡ ብዙ ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነና እዉነትም እንደሆነ፣ እንደሚያምኑም ይናገራሉ ፡፡ ነገር ግን ይህ አይነቱ እምነት ህይወታቸዉንና ኑሮአቸዉን የማይቀይር ነዉ (ያዕ 2፡14) ፡፡ ይህ አይነቱ እምነት አጋንንትም ያላቸዉ የእምነት አይነት ነዉ (ያዕ.2፡19)
ሐ. እምነት እግዚአብሔርን እንደፈለግን የምናንቀሳቅስበት እና በግላዊ ምቾታችን ላይ የተደገፈ አይደለም፡፡
መ. እምነት ተስፋም፣ መልካም መሻትም አይደለም፡፡ ተስፋ መልካም ነዉ፡፡ በትእግስትም የወደፊቱን መጠበቅ ያስችለናል ፡፡ ይሁን እንጂ እምነት ተስፋን አሁን እንዳገኘ ይቀበላል፡፡
ተስፋ የአእምሮ (የነፍስ) ሲሆን (1ተሰ.5፡8፣ ዕብ.6፡19) የነፍስ መልህቅ ነዉ፡፡ ተስፋ ልናምን በምንችልበት ስፍራ ላይ አጽንቶ ያቆመናል እንጂ ግን ያለ ተስፋ እምነት የለም፡፡
በእግዚአብሔር እምነት ሁልጊዜ በልብ ነዉ (ሮሜ. 10፡10) ፡፡
8.2. እምነት ምንድን ነዉ?
መጽሐፍ ቅዱስ እምነትን በዕብ. 11፡1 እንደሚተረጉመዉ፡-
ሀ. እምነት ማለት እግዚአብሔር የተናገረዉን ተስፋ ሁሉ እንደፈጸመዉ እርግጠኛ ሆኖ መረዳት ነዉ (The dictionary describes faith as a complete trust and confidence, firm belief without
logical proof) ፡፡
ለ. እምነት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከንን መቀበል መቻል ነዉ (ኤፌ.1፡3) ፡፡
ሐ. እምነት ተስፋዎቻችን ሁሉ እንደተቀበልን የሚያረጋግጥ በእጃችን (በልባችን) ያለ ቼክ ነዉ፡፡ (1ዩሐ. 5፡14-15፣ ማር.11፡23-24) ፡፡
መ. እምነት እግዚአብሔር የተናገራቸዉ ቃሎች ላይ ተመስርቶ የሌለዉን ማለትም በስጋ አይን ያላየነዉን እንዳለ አድርጎ መጥራት መቻል ነዉ፡፡ ይህም ማለት ነገሮች በእግዚአብሔር እንደሆኑ ማየት እንጂ በተፈጥሮ እይታ አንጻር የሚመስሉትን ማየት አይደለም (ሮሜ.4፡16-17) ፡፡ እግዚአብሔር በዘፍ.17፡5 ላይ ሲናገር የአሕዛብ አባት አደርግሃለሁ ሳይሆን አድርጌሃለሁ በማለት ነዉ፡፡ስለዚህ የእምነት አባት የሆነዉ አብርሃም በሚያደርገዉ ሁሉ በእግዚአብሔር እምነት ነበረዉ፡፡
• በአለማመን አልተጠራጠረም ፡፡
• ተስፋ የሰጠዉ እግዚአብሔር የታመነ እንደሆነ ቆጠረ ፡፡
• በእግዚአብሔር ቃል ላይ የሚቃረንን ማንኛዉንም የተፈጥሮ መረጃዎችን አልተቀበለም (ዕብ.11፡8-12፣ሮሜ. 4=16-22) ፡፡
8.3. እምነትን እንዴት እናገኛለን?
ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት እንደማንችል የተናገረዉ እርሱ እምነትንም ማግኘት የምንችልበትንም መንገድ ነግሮናል፡፡ እምነት የሌለን ከሆንን ተጠያቂ ልናደርገዉ የምንችለዉ የራሳችንን አለማወቅ እንጂ እግዚአብሔርን ሊሆን አይችለም ፡፡
እምነት የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ይመጣል (ሮሜ.10፡17) ፡፡ ከዚህ አንጻር እምነት የእግዚአብሔር ስጦታ እንደሆነ እንመለከታለን ፡፡ ‹‹ፀጋዉ በእምነት አድኗቸዋልና ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነዉ እንጂ ከእናንተ አይደለም ማንም እንዳይመካ ከስራ አይደለም (ኤፌ.2፡8) ፡፡
የእግዚአበሔር ቃል በራሱ የእምነት ቃል እንደሆነ መጽሐፍ ይናገራል፡፡ እምነትም የሚገኘዉ ይህንኑ የእምነት ቃል ከመስማት ነዉ (ሮሜ. 10=8፣14፣17) ፡፡
• ቆርነሊዎስና ቤተሰቡ መዳንን ለማግኘት የሚያስችላቸዉን እምነት በመስማት አገኙ (ዮሐ.10፡5-6፣ 11፡13)፡፡
• በልስጥራንም እግሩ የሰለለዉ ሰዉ ጳዉሎስ የእግዚአብሔርን ቃል ሲናገር ሰምቶ እንዳመነና እንደተፈወሰ (የሐ.14፡8-10)፡፡
• ከ12 ዓመትም ጀምሮ ደም የሚፈሳት ሴት የኢየሱስን ወሬ ሰምታ ተፈዉሳለች (ማር.5፡25-34)፡፡
• የእግዚአብሔርን ቃል ዘወትር ሰምተን በልባችን እንድንጠብቀዉና የሚጠቅመን እንዲሆን የእግዚአብሔር ቃል ያሳሰበናል (ምሳ.4፡20-22) ፡፡
8.4. እምነትን ማሳደግ
እምነት ልክና መጠን አለዉ (ሮሜ.12፡3-6)
• እምነት በስናፍጭ ቅንጣት ተመጥኗል
• እምነት ያድጋልም ‹‹ስለ እምነታችሁ ማነስ ነዉ›› ይላልና፡፡
እምነትን ልናሳድግበት የምንችልባቸዉን መንገዶች እንደሚከተለዉ ልናይ እንችላለን፡-
ሀ. ዘወትር የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ፣ መማርና መስማት (ምሳ. 4፡20-22) ፡፡
ለ. ዘወትር በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና በመንፈስ ቅዱስም መጸለይ (ይሁዳ 20፣1ቆሮ.14፡4) የመንፈስ ፍሬ ተብለዉ ከተጠቀሱት ዉስጥ አንዱ እምነት ነዉ፡፡
ሐ. ዘወትር በምንሰማዉ የእግዚአብሔር ቃል መሰረት ተግባራዊ ርምጃዎችን በየደረጃዉ መዉሰድን መለማመድ፡፡ እግዚአብሔር በገለጠልን በጥቂቷ ነገር ታማኝ በመሆን ካልተገበርነዉ የበለጠዉን ነገር እግዚአብሔር አይገለጥልንም ፡፡
መ. የኑሮአቸዉን ፍሬ በመመልከት በእምነታቸዉ መምሰል ይቻል ዘንድ በተቻለ መጠን ሁሉ ከእምነት ሰዎች ጋር ጊዜን ማሳለፍ (ዕብ.13፡7፣ ምሳ.13፡20) ፡፡
ሠ. የእግዚአብሔር ቃል እንደሚያስተምረን እምነት የሚሰራዉ በፍቅር ነዉ (ገላ.5፡6) ፡፡ ለምሳሌ ያህል የመቶ አለቃዉ (ማቴ.8፡5-13) እና ከነናዊቷ ሴት (ማቴ.15፡21-28) ወደ ኢየሱስ እንዲቀርቡ ያነሳሳቸዉ ጉዳይ ፍቅር ነበር ፡፡ ሁለቱም ታላቅ እምነት የነበራቸዉ እንደነበሩ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስረድቷል፡፡
ረ. የእምነት ምስክርነትን (confession) መጠበቅ (ዕብ. 10፡23፣ ሮሜ.10፡10፣ ኢያ.1፡8) ፡፡
ሰ. ዘወትር ቅድስናን መፈለግ (ዕብ.12፡14) ፡፡ የልብ ንጽህናና የይቅርታ ልብ ከሌለ የልብ እምነት እንዳይኖር አስተዋጾ ስላለዉ ነው፡፡
8.5. የእምነት ገጽታዎች
የዕብራዊያን መልእክት ምእራፍ 11‹‹የእምነት ምእራፍ›› በመባል ይታወቃል ፡፡ በምእራፍ ዉስጥ ሁለት የእምነት ገጽታዎች ተገልጸዋል፡፡ እነርሱም፡-
ሀ. የአሸናፊ ድል የመንሳት እምነት (victorious-overcomers) (1-35)
• ዳንኤል ከአንበሶች ጉድጓድ (ዳን.6)
• ሲድራቅ፣ ሚሳቅ እና አብድናጎ ከእቶኑ እሳት (ዳን.3)
• የባልቴቷ ልጅ ከሞት መነሳት (1ነገ.17)
• ዳዊት ከሰይፍ በተደጋጋሚ መዳኑ
ለ. በመከራ ጸንቶ የመታመን እምነት (faithfulness in suffering) (35-40)
• ኤርሚያስ በወህኒ (ኤር.37-38) ፤
• ኢሳያስ በመጋዝ ለሁለት ተሰንጥቆ ፤
• ሚኪያስ በጥፊ ሲመታ ፤
• ዘካርያስ እስከሞት በድንጋይ መወገር (2ዜና 24፣ማቴ23፡35-37) ፡፡
ስለዚህ እምነት ከመከራ ነጻነትን መቀበል፣ ከህመም መፈወስን እንዲሁም ለፍላጎታችን ሁሉ አቅራቦትን መቀበል ማለት ብቻ አይደለም ፡፡ እምነት እስራት በጸና ጊዜ፣ ጸሎታችን ተሰምቶ መልስ ያላገኘን በመሰለን ጊዜና ታእምራዊ አቅራቦቶችን ባላገኘን ጊዜም በመከራ ጸንቶ እግዚአብሔርን መታመን ነዉ፡፡ የቀደሙት የእምነት አባቶችም በምሳሌነታቸዉ የተመሰከረላቸዉ በነዚሁ በሁለቱም የእምነት ገጽታዎች ነበር (ዕብ. 11፡32-40) ፡፡
8.6. እምነት በአማኞች ህይወት እንዴት ሊገለጥ ይችላል?
እምነት በእግዚአብሔር ባህሪይ፣ ኃይልና በቃሉ ላይ የጸና መታመንን ይዞ አካሄዳችንን (ድርጊቶቻችንን) ከእርሱ ጋር በማድረግ ነዉ፡፡ ከዚህ አንጻር እምነት የሚገለጥባቸዉ መንገዶች የሚከተሉት ናቸዉ፡፡
• በአፍ ምስክርነት (statement of faith) (ሮሜ. 1፡5፣ ያዕ.2 14-26)
• በእምነት በመመላለስና በመኖር (2ቆሮ. 5፡7፣ ሮሜ.1፡17፣ገላ.2፡20)
8.7. የእምነት አስፈላጊነት
እግዚአብሔርን ማመን ወይም በእግዚአብሔር እምነት ለምን ያስፈልገናል?
ሀ. ያለእምነት መዳን አይቻልም (ዩሐ.3፡36፣ ኤፌ.2፡8) ፡፡ እምነት የፈዉስ፣ የአርነት አገልግሎትም ቁልፍ ነገር ነዉ፡፡
ለ. ዕብ.11፡6 እንደሚለዉ ‹‹ያለእምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤›› እኛ ደግሞ የተፈጠርነዉ ለእርሱ ደስታ ነዉ (ራዕ.4፡11፣ መዝ.147፡11) ፡፡ እርሱን ደግሞ ደስ የማናሰኝ ከሆንን የተፈጠርንበትን ዓላማ ዘንግተናል ማለት ነዉ፡፡
ሐ. በእምነት ያልሆነ ሁሉ ኃጢያት ነዉ (ሮሜ 14፡23) ፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ኃጢያትን ይጠላል፡፡ እግዚአብሔርን ማመን ባልቻልን ጊዜ ሁሉ እርሱ ሀሰተኛ እንደሆነ፣ የሰጠዉንም ተስፋ እንደማይፈጽም እየቆጠርነዉ ነዉ ያለነው ማለት ነው (ዘፍ. 23፡19) ፡፡
መ. አለማመን ወደ አለመታዘዝ ይመራናል ፡፡ የእግዚአብሔር ተስፋዎች እንዲፈጸሙ መታዘዝ አስፈላጊነዉ፡፡ለተገለጠልን የእግዚአብሔር ፈቃድ አለመታዘዝ ደግሞ በእግዚአብሔር አይን አመጽ ነዉ ፡፡
ሠ. እምነት የጻድቅ መኖሪያ ነው (ሮሜ.1፡17)
ረ. ያለእምነት በዚህች አለም ላይ በአሸናፊነትና በድል መኖር አይቻልም ዮሐ.5፡4)
ሰ. ያለእምነት ደስተኛ ሆኖ መኖር አይቻልም (1ጴጥ.1፡8-9)
ሸ. መንፈስ ቅዱስን መቀበል የሚቻለዉ በእምነት ነዉ (ገላ.3፡2)
ቀ. መጽደቅም በእምነት እንጂ በስራ አይደለም (ገላ.2፡16)
በ. ያለእምነት መጸለይም አንችልም (ያዕ.1፡6) መልስንም ከጌታ ኢየሱስ አንቀበልም (ማቴ.21፡22፡6፡11) ስለዚህ እምነት ለቁሳቁስ አቅራቦቶቻችንም ቁልፍ ነዉ፡፡
ተ. ሰውም ለመጠመቅ መጀመሪያ ማመን አለበት (ማር 16፡16) በእግዚአብሔር እምነት የሌላቸዉ ሁሉ የግድ በሌላ በአንድ ነገር ያምናሉ ማለት ነዉ፡፡ በኃይማኖት ወግ፣ በሳይንስ መረዳት፣ በተፈጥሮ መረጃዎች፣ በማስሚዲያዎች ወይም በእነዚህ ሁሉ
ቅንብር ያምናል (ሮሜ.1፡22) ፡፡ በእርግጥም ሙሉ በሙሉ በእግዚአብሔር የማያምኑ ሁሉ በአንድ ስፍራ በዳቢሎስ አምነዉ ራሳቸዉን ያገኙታል ፡፡ ሰይጣን እንዳለ ባለማመን እንኳን እያለ ሰዉ ሰይጣን የሚለዉን ማመንም ይቻላል ማለት ነዉ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር በእርሱና በሚለን እንድናምን መፈለጉና መጠበቁ ጻድቅ ነዉ፡፡ እዉነትን ሊነግረን፣ ሊረዳንና ለህይወት ጥያቄዎቻችን
ሁሉ መልስን ሊሰጠን እርሱ የታመነ ነዉና፡፡
8.8. እምነትን በተግባር (በሥራ) ላይ ማዋል
መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን እዉነተኛ የተፈተነ እምነት ‹‹በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋዉ ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር›› እንደሆነ ነዉ (1ጴጥ.1፡7) ፡፡ ስለዚህ በእምነት ህይወታችን ላይ ሊመጡ የሚችሉ ፈተናዎች እንዳሉ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ እምነትን በተገቢዉ መንገድ በተግባር ላይ ለማዋል የምንችለዉ፡-
ሀ. በማንኛዉም ጉዳዮቻችን በተመለከተ በእግዚአብሔር ቃል ዉስጥ የተገባልልን ኪዳን /ተስፋ መያዝ (ፊልጵ.4፡19፣2ቆሮ.1፡20) ፤
ለ. ተስፋዉ /ከኪዳኑ ጋር የተያያዙትን ቅድመ ሁኔታዎችን መፈጸም/ (1ዮሐ.5 ፣ዘዳ፡28፡1-3፣15፣ሚል.3፡7-12 (10) ፣ ማር.11፡24-25)፤
ሐ. የተስፋ ቃሎቻችን አምነን መናገራችንን (confession) ባለማቋረጥ መቀጠል ፤
መ. የሰማነዉን ቃል አድራጊዎች መሆን (ያዕ.1፡22-23፣ ዮሐ.9፡7፣ያዕ.2፡20-24) ፤
ሠ. ያመነዉንና የያዝነዉን እምነት በተግባር መለማመድ (ማቴ.9፡20-22 ፣14፡25-29) ፤
ረ. በራስ ማስተዋል አለመደገፍ (ምሳ.3፡1-6፡1ጢሞ.1፡4-7፡620-21፣ 2ጢሞ. 2፡16-18፣
ሮሜ.14፡1፣ቆላ.2፡8)
ሰ. ሰው ሲጠመቅ ያመነውን በሥራ ገለጸው ማለት ነው፡፡
8.9. የእምነት ጠላቶችን ድል መንሳት
እምነት በአማኞች ሕይወት እንዳይሰራና እንዳያድግ ከሚያደርጉት የእምነት ጠላቶች ዋናዎቹን እንደሚከተለዉ እንመለከታለን፡-
ሀ. አለማወቅ፡- ማንም ሰዉ ያልሰማዉንና ያላወቀዉን ተስፋ/ኪዳን ከእግዚአብሔር ዘንድ ሳይኖረዉ እምነት ሊኖረዉ ወይም እምነቱ ሊዳብር አይችልም ፡፡ ለዚህ ደግሞ መፍትሄዉ የእግዚአብሔርን ቃል ማጥናትና ማሰላሰልን ይጠይቃል ፡፡
ለ. ፍርሃት፡- ፍርሃት ክፉና መጥፎ ነገር ይደርስብኛል ብሎ በእዉነት ዕውቀት ላይ ያልተመሰረተ አሉታዊ ስሜት ነዉ (fear= false
evidence appearing real) ፡፡ በእግዚአብሔር አባታዊ ጥበቃ እና ፍቅር ላይ መታመን ያስፈልጋል (1ዮሐ.4:18) ፡፡