ጊዜው አሁን ነው!

ጥበብን የተሞላ ልብ ይኖረን ዘንድ ፣ እድሜያችንን መቍጠር አስተምረን፡፡ መዝሙር 90፡12
በምድር ያለን ጊዜ ምን ያህል አጭር እንደሆነ በተረዳን መጠን ጊዜያችንን በአግባቡ ለመጠቀም እንተጋለን፡፡ የምድር ኑሮዋችን አጭር መሆኑን እስካላስታወስን ግን በተለያዩ ምክኒያቶች የምናባክነው ይበዛል፡፡
አቤቱ፥ ፍጻሜዬን አስታውቀኝ፥ የዘመኔ ቍጥሮች ምን ያህል እንደ ሆኑ፥ እኔ ምን ያህል ወደ ኋላ እንደምቀር አውቅ ዘንድ። መዝሙር 39፡4
በምድር ላይ ያለን ጊዜ የተሰጠንን ስራ ለመጨረስ የሚበቃ እንጂ ምንም የሚባክን ትርፍ ጊዜ የለንም፡፡ በጊዜ አስተዳደራችን እጅግ የተሳካልን ብንሆን ጊዜያችንን ሙሉ ለሙሉ ብንጠቀምበት ነው፡፡ የልባችንም ጩኸት በምድር ላይ ምን ያህል እንደምንኖር ማወቅ ነው፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ በምድር ለይ የምንኖረው ለአጭር ጊዜ እንደሆነ ይናገራል፡፡
ሰው ከንቱን ነገር ይመስላል፤ ዘመኑ እንደ ጥላ ያልፋል። መዝሙር 144፡4
ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። ያዕቆብ 4፡14
እርግጥ ነው እግዚአብሄር በምድር ያለን ጊዜ አጭር እንደሆነ ይነግረናል እንጂ የሚቀረንን ቀን ምን ያህል እንደሆነ ቁጥሩን አይነግረም፡፡
እኛም የሚያስፈፈልገን ነገር ዛሬ ብቻ የእኛ እንደሆነና ዛሬን በሚገባ መጠቀም እንዳለብን ማወቅ ነው፡፡ ዛሬን በሚገባ እስከተጠቀምንበት ድረስ ህይወታችንን ሁሉ በሚገባ እንጠቀምበታለን፡፡
በዛሬ ስኬታማ ከሆንን በህይወት ዘመናችን ሁሉ ስኬታማ እንሆናለን፡፡ አንዳንዴ ነገ ለጌታ ለመኖር ልዩና የተሻለ እድል ይዞልን እንደሚመጣ እናስባለን፡፡እንደዚያ በማሰብ በዛሬ ላይ ካለአግባብ እንዝናናለን፡፡ ነገ ግን ምን እንደሚያመጣ አናውቅም፡፡ ነገ ካሰብነው በላይ ተግዳሮቶችን ይዞ ሊመጣ ይችላል፡፡ ዛሬንም ነገንም በሚረዳን በእግዚአብሄር እንጂ በነገ መመካት የለብንም፡፡
. . . ነገ የሚሆነውን አታውቁምና። ያዕቆብ 4፡13
ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ። ምሳሌ 27፡1
መፅሃፍ ቅዱስ በግልፅ የምድር ጊዜያችን አጭር እንደሆነ ደጋግሞ ይነግረናል፡፡ በከንቱ የምንዝናናበትና የምናባክነው ትርፍ ጊዜ ጊዜ የለንም፡፡ ተርፎን የምናባክነው ምንም ጊዜ የለም፡፡
አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ነገን ወደዛሬ አምጥተንም መኖር እንፈልጋለን፡፡ እግዚአብሄር ቀኑን ጊዜውን እንደከፋፈለው ሁሉ በህይወት ያሉትን ስራዎቻችንን በጊዜ ከፋፍሎዋቸዋል፡፡ ነገን ዛሬ ላይ አምጥተን ለመኖር መሞከር ጥበብ አይደለም፡፡ የነገን ተግዳሮት ዛሬ ለመፍታት መሞከር ህይወትን ካለአግባብ ለመቆጣጠር መሞከር ነው፡፡ ጠቢብ ለነገ ዛሬ ያቅዳል ነገር ግን የነገን ለነገ ትቶ የዛሬን ዛሬ ይሰራዋል፡፡ ዛሬን ለመኖር ያለን ዛሬ ብቻ ነው፡፡
እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤ . . . ዘመኑን ዋጁ። ኤፌሶን 5፡15-16

Published by

wongelu

Name: Wongelu Woldegiorgis Nationality: Ethiopian Profession: Naturopathic Doctor Nutritionist Accountant Entrepreneur Formulator of beauty and wellness products Consultant for business development and legal documentation Education: BSc in Acvounting, Master’s Degree in Nutrition, Marketing Management . Honorary Doctorate from Abyssinia, Ethiopia PHD Naturopathic Medicine – Languages: Amharic, English, Swahili Personal Qualities: Honest, adaptable, good communicator, spiritually devoted, passionate about natural health and community development Church Involvement: Active in Apostolic Church International Fellowship Limited (ACIF Uganda) Talents: Translation, teaching, preaching, and serving in children's ministry Preparing curriculum and lesson plans based on Oneness Apostolic doctrine Other Interests: Passionate about fitness and bodybuilding Pursuing online work in writing, translation, virtual assistance, and e-commerce

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *