የየዋህነት ክብር

የጌታም ባሪያ ለሰው ሁሉ ገር ለማስተማርም የሚበቃ ለትዕግሥትም የሚጸና ሊሆን እንጂ ሊጣላ አይገባውም። ደግሞም፦ ምናልባት እግዚአብሔር እውነትን ያውቁ ዘንድ ንስሐን ይሰጣቸዋልና ፈቃዱን ለማድረግ በዲያብሎስ ሕያዋን ሆነው ከተያዙበት ወጥመድ ወጥተው፥ ወደ አእምሮ ይመለሳሉ ብሎ የሚቃወሙትን በየዋህነት ይቅጣ። 2ኛ ጢሞቴዎስ 2፡24-26
የዋህነት የመንፈስ ፍሬ እንደሆነና መንፈሳዊ ውጤታችንና ፍሬያማነታችነ የሚለካበት ወሳኝ ባህሪ እንደሆነ መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡
የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው። ገላትያ 5፡22
በነገር ሁሉ ምሳሌያችን የሆነው ኢየሱስ የዋህ ነበረ፡፡ ከእኔም ተማሩ ብሎ ያስተምረናል፡፡
ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ ማቴዎስ 11፡29
የዋህነት የጥሪያችን ደረጃ ነው፡፡ ከየዋህነት ያነሰ ኑሮ እንድንኖር አልተጠራንም፡፡ ለጥሪያችን እንደሚገባ መኖር በየዋህነት መኖር ነው፡፡
እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤ በትሕትና ሁሉና በየዋህነትበትዕግሥትም፤ እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሡ፤ ኤፌሶን 4፡1-2
ስለየዋህነት መፅሃፍ ቅዱስ ብዙ ያስተምራል፡፡ ለምሳሌ ያህል ይህን ያህል ስለ የዋህነት አስፈላጊነት ካየን የየዋህነትን ትርጉም እንመልከት፡፡
ግን የዋህነት ምንድነው?
የዋህነት በብዙ ቃላት ሊተረጎም የሚችል ቃል ነው፡፡ የየዋህነትን ትርጉም እንመልከት፡-
ቸር
መልካምና ርህሩህ አዛኝ ስለሌላው ግድ የሚለው
ክፉና ግፈኛ ያልሆነ
ለሰው የሚጠነቀቅ ፣ ግዴለሽ ያልሆነ ፣ ራስ ወዳድ ያልሆነ ፣ የሰውን ፍላጎት የሚያከብር
ልከኛ
ለጥቅም የማይስገበገብ ፣ በቃኝ የሚል ፣ ለመኖር ብዙ ነገር የማይጠይቅ
የተከበረ
ሰዎች የሚያከብሩት ፣ ክብሩን ጠብቆ የሚኖር ፣ የሚያዋርደውንና የሚያስንቀውን ክፉ ነገር የማያደርግ
ጨዋ
የተገራ ፣ ለጥቅም የማይጣላ ፣ በራስ ወዳድነት የማይከራከር
ሰላማዊ
ሰላም ያለው ፣ ለሌላም ሰላም የሚሰጥ ፣ አስጊ ያልሆነ
አክባሪ
ሰውን አክባሪ ፣ ሰውን የማይንቅ ፣ ለሰው ትልቅ ስፍራ ያለው
ጭምት
ረጋ ያለ ፣ የማይቸኩል ፣ ቁጥብ ፣ ስሜቱን የሚገዛ
በተራ ነገር ላይ የማይገኝ
በትክክለኛው መንገድ የማይመጣን ጥቅም የሚንቅ ፣ ነውረኛ ረብ የማይወድ
ደረጃው ከፍ ያለ
መልካም ባህሪ ያለው በሚሉት ቃላት ሊገለፅ ይችላል፡፡
እኛ የምንሰራው ከፍ ላለ ነገር ነው፡፡እኛ የምንሰራው ለመንግስቱ ነው፡፡ እኛ የምንፈልገው የእግዚአብሄርን ፅድቅ ነው፡፡ ሌላ ሁሉ በእግዚአብሄር የሚጨመርልን የእግዚአብሄር ቤተሰብ አባላት ነን፡፡

Published by

wongelu

Name: Wongelu Woldegiorgis Nationality: Ethiopian Profession: Naturopathic Doctor Nutritionist Accountant Entrepreneur Formulator of beauty and wellness products Consultant for business development and legal documentation Education: BSc in Acvounting, Master’s Degree in Nutrition, Marketing Management . Honorary Doctorate from Abyssinia, Ethiopia PHD Naturopathic Medicine – Languages: Amharic, English, Swahili Personal Qualities: Honest, adaptable, good communicator, spiritually devoted, passionate about natural health and community development Church Involvement: Active in Apostolic Church International Fellowship Limited (ACIF Uganda) Talents: Translation, teaching, preaching, and serving in children's ministry Preparing curriculum and lesson plans based on Oneness Apostolic doctrine Other Interests: Passionate about fitness and bodybuilding Pursuing online work in writing, translation, virtual assistance, and e-commerce

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *