እግዚአብሔርን ማወቅ ….1…..

“….በሕይወትም ትኖራላችሁ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።” ሕዝ ፴፯፣፮
በሕይወት የመኖራችን ዓላማ እግዚአብሔርን ማወቅ ከሆነ እግዚአብሔርን እናውቀዋለን ወይ?


ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን፥ ከሚቃጠልም መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እወድዳለሁና። ሆሴዕ ፮፣ ፮
፩. እግዚአብሔርን ማወቅ ያለብን ለምንድን ነው?
– ለሕይወት ስኬት – ለምድራዊ አስቤዛ ኑሮ መሟላት?
– ከኑሮ ጭንቀት ለመላቀቅ – ሰላምና እረፍት ለማግኘት?
– ለጠቅላላ ዕውቀት/ለመረጃ? – አለ ወይስ የለም? እውነቱን ለማወቅ-

እግዚአብሔር ሲባል – ወደ አእምሮአችን / ወደ ምናባችን የሚመጣው ምስል ምንድን ነው?
o በሩቅ በሰማይ ያለ- ቁልቁል የሚያይ ሽማግሌ መሰል……?
o ወይም ሌላ ምስል…….?

እግዚአብሔርን ስናስብ ትዝ የሚለን ምንድን ነው?
– እግዚአብሔርን ወይስ ከእግዚአብሔር የሆኑ ነገሮችን፤
– እግዚአብሔር በሕይወታችን በኃይሉ እየሠራ ነው? ወይስ
በአእምሮአችን እንዲሁ የተቀመጠ ከብዙ ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው?
– እግዚአብሔርን ነው ወይስ ስለእግዚአብሔር ነው የምናውቀው?
ስለጃንሆይ ልናውቅ እንችላለን፤ ጃንሆይን ግን ላናውቃቸው እንችላለን፤ አላየናቸውም፣ አላገኘናቸውምና።
– እግዚአብሔርን እናውቀዋለን? – እርሱስ ያውቀናል? – እንተዋወቃለን?
– እናናግረዋለን? – ከሆነስ — ይሰማናል? — ይመልስልናል? – እንደሚመልስልን ይሰማናል?
ከእነዚህ ጥያቄዎች አንዱ መልሳችን «አይ» ከሆነ – እግዚአብሔርን አላወቅነውም። ወይም ስለእግዚአብሔር ያወቅነው አልገባንም።

– እግዚአብሔር ሊታወቅ ይችላል? ወይስ አይችልም? –
የምታመልኩትን እየተመለከትሁ ሳልፍ። ለማይታወቅ አምላክ የሚል ጽሕፈት ያለበትን መሠዊያ ደግሞ አግኝቼአለሁና። እንግዲህ ይህን ሳታውቁ የምታመልኩትን እኔ እነግራችኋለሁ። የሐዋ ፲፯፣ ፳፫
እናንተስ ለማታውቁት ትሰግዳላችሁ፤ እኛ መዳን ከአይሁድ ነውና ለምናውቀው እንሰግዳለን። ዮሐ ፬፣፳፪

እግዚአብሔርን የምናመልከው አውቀነው ነው? ወይስ ባይገባንም ማምለክ ስላለብን? ወይስ እንዲሁ በዘልማድ ሌሎች ስላደረጉት?

እግዚአብሔርን ማወቅ/አለማወቅ ያለው ተጽእኖ
– በሕይወታችን ለነገሮች ቅድሚያ የምንሰጠው ካለን የእግዚአብሔርን እውቀት አንጻር ነው።
በደንብ ካወቅነው/ከገባን እንኖርለታለን። እንኖርበታለን። — ካልሆነ እንደ ትርፍ/ተጨማሪ እናየዋለን።
– በሕይወታችን በሚገጥሙን ፈተናና እና ችግሮች የምንወስዳቸው ውሳኔዎች እግዚአብሔርን ምን ያህል እንደምናውቀው ያሳያሉ።
– ሕይወትን ለመኖር የሚያስመኘው ስኬቶቻችን ናቸው – ወይስ በዓላማ መኖራችን?
የዚህ ዓለም ስኬት መጨረሻው ምንድን ነው?.. ምን ስናገኝ ነው በቃ የምንለው?
– በየዕለቱ/ በየጊዜው አእምሮአችን የሚይዘው ምንድን ነው? በልባችን እና በአእምሮአችን ሰፊውን ስፍራ የያዘው እግዚአብሔርን ከማወቅ / ካለማወቅ ጋር የሚያያዝ ነው።

አንድ ባለሃብት ለአንድ አገልጋይ ያለውን ሰፊ የልማት/ የእርሻ ቦታ ሲያስጎበኘው ከስፋቱ የተነሳ በአንድ ቀን ተጎብኝቶ ሊያልቅ አልቻለም። ኋላ ባለሃብቱ «እንዴት ነው? ምን ተሰማህ?» ብሎ የሙገሳ ቃል ሲጠብቅ አገልጋዩ፡ «ይህንን ሁሉ ሃብት ለማስተዳደር ልብህ በዚህ ስለሚጠመድ ያሳዝነኛል» አለው።
የዚህ ባለሃብት ልብ አሁን እየኖረበት ካለ ዓለም ጋር የተቆራኘ ነው።
ለአሁኑ እና ለዘላለሙ፣ ላለውና ለሚመጣው ነገር ሁሉ የምንሰጠው ዋጋ/ቦታ ባለን የእግዚአብሔር ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ነው።
……………ይቀጥላል…………..

Published by

wongelu

Name: Wongelu Woldegiorgis Nationality: Ethiopian Profession: Naturopathic Doctor Nutritionist Accountant Entrepreneur Formulator of beauty and wellness products Consultant for business development and legal documentation Education: BSc in Acvounting, Master’s Degree in Nutrition, Marketing Management . Honorary Doctorate from Abyssinia, Ethiopia PHD Naturopathic Medicine – Languages: Amharic, English, Swahili Personal Qualities: Honest, adaptable, good communicator, spiritually devoted, passionate about natural health and community development Church Involvement: Active in Apostolic Church International Fellowship Limited (ACIF Uganda) Talents: Translation, teaching, preaching, and serving in children's ministry Preparing curriculum and lesson plans based on Oneness Apostolic doctrine Other Interests: Passionate about fitness and bodybuilding Pursuing online work in writing, translation, virtual assistance, and e-commerce

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *