መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት እናጥና?

ሰዉ ከእግዚአብሔር ከሚሰማበትና ከሚያደምጥበት መንገዶች ዋናዉ ቃሉን ማጥናት ነዉ፡፡ እግዚአብሔርም ራሱን ለሰዎች የሚገልጠዉ በቃሉ ነዉ (1ኛሳሙ.3፡21) ፡፡ መጸሐፍ ቅዱስ የተጻፈዉ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት በመሆኑ እንደ ሌሎች መጻህፍት በማንበብ ብቻ ልንረዳዉ ስለማንችል የእግዚአብሔር ገላጭነት አስፈላጊ ነዉ፡፡ ስለዚህ መጸሐፍ ቅዱስን ማጥናት ሲያስቡ
በቅድሚያ ቃሉን ለማጥናት አእምሮዉን በመሰብሰብና አካባቢዎም ከረብሻ የጸዳ ቢሆን ይመረጣል፣ ቃሉን ሲያነብቡ ምስጢሩ እንዲገባዎት የቃሉን ባለቤት እውነቱን እንዲገልጥልዎት ይጸልዩ (መዝ. 118፡17-18) ፡፡
አስቀድመን እንደተመለከትነዉ ቃሉ በሕይወታችንም እንዲሰራና የሚሰጠንንም ጥቅም ለማግኘት የሚከተሉትን ዋናዋና መርሆች በመጠቀም መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት ያስፈልገናል፡፡
ሀ. ቃሉን ለማጥናት ጊዜን መስጠት (ዕዝ.7፡10)
ለ. የቃሉን መንፈስና ዕዉነት በመግለጥ እንዲናገረንና እንዲያስረዳን አስተማሪ የሆነዉን የእግዚአበሔርን መንፈስ በጸሎት መጋበዝ (ዮሐ.14፡26፣16፡13-15)
ሐ. የልብ ፍላጎትና ፈቃደኝነት ይኑረን (1ኛጴጥ.2፡1-3፣የሐዋ.17፡10-11፣ኤር.15፡16)
መ. ማስተዋል (ዕብ.4፡1-2፣ማቴ.13፡14-15፣ኢያ33፡14፣37፡5፣የሐዋ.8፡27-31)
ሠ. በእነዚህ መንገዶች ያጠናነዉን ቃል፡-
• እናሰላስለዉ (meditation of the word)
• ትዝታችንም ይሁን (memorization of the word)
• ለግል ህይወትህ እንዲናገርህ ራስህን በማዘጋጀት የሚከተሉትን ጥያቄዎች ጠይቅ፡-
1. በማነበዉ ክፍል ዉስጥ ያለዉ ሃሳብ የእኔን ህይወት የሚመስልበት ሁኔታ አለን ?
2. ልከተለዉ የሚገባኝ ትምህርት፣ ምክር ወይም መመሪያ አለን ?
3. እንድናዘዘዉና እንድተወዉ የሚያሳየኝ ኃጢአት አለን ?
4. እንድጠብቀዉ የሚያሳየኝ ተስፋ አለን ?
5. ሌሎች ላስታውሳቸው የሚገባኝ እዉነቶች በዚህ ክፍል ዉስጥ አሉን?
ረ. ያገኘኸዉን መልእክት አጭር እና ግልጽ አድርገህ በማስታወሻህ ላይ ጻፈዉ
ሰ. የተገለጠልህን እዉነት ተግተህ ታዘዘዉና ተግብረዉ (1ኛሳሙ.15፡22-23፣ያዕ.1፡22-25፣ዮሐ.8፡31-32)
ሸ. እንደአስፈላጊነቱ ለሌሎች አካፍለዉ፡፡
እንግዲህ በዚህ መንገድ ቃሉን ተረጋግተዉ ማጥናት የሚችሉ ሲሆን ከመጸሐፍ ቅዱስ ጋር ያለዎት
ዝምድና ቀላል እንዲሆን የብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን መጸሐፍት ዝርዝርን በቃል ቢያጠኑ ቶሎ ብለዉ የሚፈልጉትን ለመግለጽና ለማውጣት አይቸገሩም ፡፡ በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥሮችን ቢያጠኑ ጥሩ ነዉ፡፡ ቁጥሮቹን ለማጥናት ብዙ ሳይደክሙ፡-
ከ1-10 እና 20፣ 30፣ 40፣ 50፣ 60፣ 70፣ 80፣ 90፣ 100 እና 1000 እንዴት ዓይነት ቅርጽ እንዳላቸዉ ለይተዉ ይወቋቸዉ፡፡
1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 8፣ 9፣ 0፣ !፣ “፣ #፣ $፣ %፣ &፣ ‘፣ (፣ )፣ *
3.1. የተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴዎች
መጽሐፍ ቅዱስ በመጀመሪያ ሲጻፍ ምንባቡ የነበረውን ትክክለኛ ትርጉም ለማግኘት የተቻለውን ሁሉ ጥረት ማድረግ ከአጥኚው ይጠበቃል፡፡ ይህም አጥኚው ከልዩ ልዩ አውዶች አንጻር ማየትን ያካትታል፡፡
ምሳሌ፡-
• ታሪካዊ ዐውድ
• ባህላዊ ዐውድ
• ቋንቋዊ ዐውድ
• ፖለቲካዊ ዐውድ
• ማህበራዊ ዐውድ
• ኃይማኖታዊ ዐውድ
መጸሐፍ ቅዱስን ሰዎች በተለያየ መንገድ ሊያጠኑ ይችላሉ፡፡ አጠናንዎን በተለያየ መንገድ እስኪያሰፋ ግን በእነዚህ በሶስት መንገዶች ማጥናት ቢችሉ ይመረጣል፡፡
3.2. ሶስቱ የጥናት መንገዶች
ሀ. ምዕራፍ በምዕራፍ የመጸሐፍ ቅዱስ ጥናት ፣
ለ. በሰዎች ሕይወት ላይ የተመረኮዘ ጥናት ፣
ሐ. በተወሰነ ርዕስ ላይ የሚደረግ ጥናት ናቸዉ፡፡
ሀ/ ምዕራፍ በምዕራፍ የመጸሐፍ ቅዱስ ጥናት ከመጸሐፍ ቅዱስ አንድን መጸሐፍ በመዉሰድ በየእለቱ አንድ ምዕራፍን ሲወስኑ እነዚህን መሰረታዊ ጥያቄዎች በመጠየቅ ማጥናት ይቻላል፡፡
• ለምዕራፉ ምን ርዕስ ይሰጠዉ
• በምዕራፉ ዉስጥ የተሰጡ ዋናዋና ትምህርቶች ምንድን ናቸዉ
• በምዕራፉ ዉስጥ ልብህን የነካዉ ጥቅስ ምንድን ነዉ ጽፈህ በቃልህ እስክትይዘዉ ድረስ ደጋግመህ አጥናዉ
• በምዕራፉ ዉስጥ የተጠቀሱትን ዋናዋና ሰዎችን ጥቀስ
• በምዕራፉ ዉስጥ ስለ አማላክ ማንነነት ባህርይ የተጠቀሰ ካለ ግለጽ
• እኔ ልከተለዉ የሚገባኝ ምሳሌ ምንድን ነዉ
• እኔ ላስወግደዉ የሚገባኝ ስህተት ምንድን ነዉ
• እኔ ልፈጽመዉ የሚገባኝ ትዕዛዝ ምንድን ነዉ
• እኔ ልይዘዉ የሚገባኝ የተስፋ ቃል ምንድን ነዉ
• በዚህ ምዕራፍ መሰረት ልጸልየዉ የሚገባኝ ጸሎት ምንድን ነዉ
በእነዚህ ከላይ በተሰጡት መጠይቆች መሰረት በማጥናት ማወቅ የሚቻል ሲሆን የተሰጡትን ጥያቄዎች በሙሉ በምዕራፍ ዉስጥ ላይመለስ ይችላል፡፡
ለ/ በሰዎች ህይወት ላይ የተመሰረተ ጥናት
በመጸሐፍ ቅዱስ ዉስጥ 2330 ሰዎች ገደማ ተጠቅሰዋል ፤ ከእነዚህም ብዙዎቹ የህይወት ታሪካቸዉን በመከታተል ብዙ ትምህርት ልናገኝ እንችላለን፡፡ ከመጽሐፍ ቅዱስ የሆነ የሰዎችን ወይም የስፍራን ስም በመዉሰድ ማጥናት ፣ ለምሳሌ ፡- “ሄሮድስ” ይህ ስም ስንት ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ዉስጥ ተጠቅሷል መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ ሰዉ ምን ይላል ? ይህ ማለት የአንድን ሰዉ (ገፀ ባህሪይ) የህይወት አቋሙን ማጥናት ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ፡- ስለ “ዳዊት” — ከእግዚአብሔር ጋር የነበረዉን ግኑኝነት፣ ለእግዚአብሔር መሰጠቱ፣ የሠራዉ መልካምነት ወዘተ.
በዚህ ጥናት ዉስጥ የሰዎቹን ስምን ትርጉም ለማወቅና ታሪኩ ጎልቶ እንዲገባን የመጸሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት በተጨማሪ ቢኖረን ይመርጣል፡፡ ይህን ጥናት ለማጥናትም ከዚህ በታች ያሉትን ጥያቄዎች መመለስ ያስፈልጋል፡፡
• ስለሰዉየዉና ስለቤተሰቡ ምን ተጻፈ
• በወጣትነቱ ዘመን ምን አከናወነ
• በህይወቱ ዘመን የገጠመዉ ፈተና ምን ነበር እንዴትስ ተወጣዉ
• ሰዉየዉ ከእግዚአብሔር ጋር በነበረዉ ግንኙነት የታየዉን ስጋዊ ድክመት ይግለጹ
• በእምነቱ ጽናት የተገለጸዉ የእግዚአብሔር ክብር ምንድን ነዉ
• ጓደኞቹ እነማን ነበሩ ጓደኞቹ በህይወቱ ላይ ምን አይነት ለዉጥ አመጡ
• በህይወት ዘመኑ የተሳሳታቸዉ ነገሮች ምንድን ናቸዉ
• ሰውየው ክርስቶስን ይመስል ነበር ወይስ አይመስልም
• በሰዉየዉ ህይወት ላይ ይታዩ የነበሩ መልካም ስነምግባሮችን ይግለጹ
• ከዚህ ሰዉ ህይወት ያገኙትንና ለትምህርትዎ የሚሆኑ ዋናዋና አሳቦችን ይግለጹ
በጥናቱ መሰረት ጸሎትን ይጸልዩ፡፡
ሐ. በተወሰነ ርዕስ ላይ የሚደረግ ጥናት
ይህ ጥናት ደግሞ ከመጸሐፍ ቅዱስ ዉስጥ ልታጠናዉ የፈለግነውን አንድን ርዕስ (topic) በመዉሰድ በርዕሱ መሰረት ሰፊ ጥናትን ማካሄድ ነዉ፡፡ ለምሳሌ፡- ጸሎት፣ ንስሃ፣ ቅድስና፣ ፍቅር፣ እምነት፣ ወዘተ … ለዚህ ጥናትም የተለያዩ የማጥኛ መረጃ እንደ የመጸሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላትና ሌሎች ኮሜንታሪ መጽሐፍትን፣ እንዲሁም የመጸሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ማዉጫ ቢኖርም ይመረጣል፡፡
የሚፈልጉትን ርዕስ ከመረጡ በኋላ በተለያየ ስፍራ ስለ ርዕሱ የተሰጡትን ጥቅሶች በማገናዘብ ማጥናት ይቻላል፡፡
ለምሳሌ፡- ርዕስ፡- ጸሎት፤
– ወደ ማን እንጸልይ
– መቼ እንጸልይ
– እንዴት እንጸልይ
– ምን እንጸልይ ወዘተ የመሳሰሉትን ጥያቄዎች በመመለስ ጥናትዎን ያስፉት፡፡
በአጠቃላይ እነዚህን የግል የመጸሐፍ ቅዱስ ማጥኛ ዘዴዎችን መጠቀም የሚቻል ሲሆን እዉቀትዎን የበለጠ ለማስፋት በአጥቢያዎ የሚሰጡትን የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርችን ቢከታተሉ ያግዝዎታል፡፡

Published by

wongelu

Name: Wongelu Woldegiorgis Nationality: Ethiopian Profession: Naturopathic Doctor Nutritionist Accountant Entrepreneur Formulator of beauty and wellness products Consultant for business development and legal documentation Education: BSc in Acvounting, Master’s Degree in Nutrition, Marketing Management . Honorary Doctorate from Abyssinia, Ethiopia PHD Naturopathic Medicine – Languages: Amharic, English, Swahili Personal Qualities: Honest, adaptable, good communicator, spiritually devoted, passionate about natural health and community development Church Involvement: Active in Apostolic Church International Fellowship Limited (ACIF Uganda) Talents: Translation, teaching, preaching, and serving in children's ministry Preparing curriculum and lesson plans based on Oneness Apostolic doctrine Other Interests: Passionate about fitness and bodybuilding Pursuing online work in writing, translation, virtual assistance, and e-commerce

2 thoughts on “መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት እናጥና?”

Leave a Reply to Asrat Chinasho Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *